የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል-ተገልጋዮች

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ ፣ሚያዚያ 26/2018 (ኢዜአ)፦መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩ እንግልትን በማስቀረት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮልናል ሲሉ የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

በማዕከሉ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ፍቃድ ለማውጣት የመጡት አቶ ፍቃዱ ባይሳ ለኢዜአ እንዳሉት ፤ አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ የተደገፈና ከወረቀት ንክኪ የፀዳ በመሆኑ ጉዳያቸውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ ችለዋል።


በተለይ ሁሉንም ዓይነት አገልግሎት በአንድ ስፍራ በተሟላና ቀልጣፋ በሆነ አግባብ ማግኘት መቻላቸው ከዚህ በፊት የነበረውን አላስፈለጊ ወጪና እንግልት እንዳስቀረላቸው ነው የሚናገሩት።

የመሬት ይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ ለሙውሰድ ወደ ማእከሉ መምጣታቸውን የሚናገሩት ወይዘሮ ብርቄ ጣሶ ፤በማዕከሉ የሚፈልጉትን አገልግሎት በፍጥነት ለማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል።


በተለይም በአንድ ቦታ የተሟላና ፈጣን አገልግሎት ማግኘት መቻሉ ከዚህ በፊት ይገጥሙ የነበሩ ችግሮችን እንዳስቀረ ነው ያነሱት።

ጉዳያቸውን በአጠረ ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን የገለጹት ደግሞ የመኖሪያ ቤት የሊዝ ውል ስምምነት ለመፈጸም ወደ ማእከሉ የመጡት አቶ ጂረኛ ተረፈ ናቸው።


አገልግሎት አሰጣጡም ቀልጣፋ፣ምቹ እና ድካምን ያስቀረ ሆኖ እንዳገኙትም ነው የተናገሩት።

የአምቦ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አራርሳ ከበደ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ በአንድ ቦታ 107 አገልግሎቶችን መስጠቱ ማሕበረሰቡ ይደርስበት የነበረውን እንግልት ለማስቀረት አስችሏል ብለዋል።


በተለይም በዘርፉ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ይነሱ የነበሩ በርካታ ቅሬታዎችን ለመፍታት እንዳስቻለም ነው የተናገሩት።

በማዕከሉ የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት፣ ግልፅና ቀልጣፋ ለማድረግና የተገልጋዮችን እርካታን በተሻለ መልኩ ለመጨመር በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በማዕከሉ 18 የከተማው ሴክተር ጽህፈት ቤቶች 107 አገልግሎቶችን በተሟላ መልኩ እየሰጡ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026