የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የጂንካ ከተማ ዲጂታላይዝድ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ተገልጋዮች በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን እንዲፈጽሙ አስችሏል

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ሰኔ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የጂንካ ከተማ ዲጂታላይዝድ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ተገልጋዮች በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን እንዲፈጽሙ ማስቻሉ ተገለጸ፡፡

የከተማው የአንድ ማዕከል ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በከተማዋ ቀደም ሲል በአሰራር ሲስተዋል የነበረውን ችግር በመፍታት የተገልጋዮችን እንግልት ማስቀረቱን ባለጉዳዮች ተናግረዋል።

የአገልግሎት አሰጣጡን አስመልክቶ ኢዜአ ካነጋገራቸው ተገልጋዮች መካከል አቶ ስሜነህ ካሳሁን እንደገለፁት፤ የማዘጋጃ ቤቱ የቀደመ አሰራር ኋላ ቀር በመሆኑ ተገልጋዩን ለውጣ ውረድ ሲያጋልጥ ቆይቷል።

ይህን ችግር ለመፍታት በአሁኑ ወቅት የተጀመረው የአንድ ማዕከል ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በዲጂታል ታግዞ መሰጠቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ለመፈጸም እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

ሌላኛው የማዘጋጃ ቤቱ ተገልጋይ አቶ አሊ ሙሐመድ በበኩላቸው፤ በአንድ ማዕከል ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የታዩ የአሰራር ለውጦችን ወደ ሌሎች ተቋማት ማስፋት እንደሚገባ ተናግረዋል።

አገልግሎቱ ከቢሮክራሲና ሙስና የፀዳ መሆኑ ቀደም ሲል በአገልግሎት አሰጣጥ ይስተዋል የነበረን የመልካም አስተዳደር ችግር መፍታቱንም አመልክተዋል።

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት የአንድ ማዕከል አስተባባሪ አቶ ተመስገን ጋናቡል በበኩላቸው፤ የማዘጋጃ ቤቱን አሰራር ለማዘመን ለሰው ሀይል ልማትና ለቴክኖሎጂ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።

ማዘጋጃ ቤቱ ቀደም ሲል በወረቀት አገልግሎቶችን ሲሰጥ በነበረባቸው ወቅቶች ፋይል ከመጥፋት ባለፈ በተገቢው ባለመደራጀት ለፍለጋ ሲወስድ የነበረን ረጅም ጊዜ ለማስቀረት ወደ ዲጂታል የምዝገባ ስርአት መግባቱን ጠቁመዋል።

በዲጂታል ቴክኖሎጂው የአንድ ተገልጋይ ጉዳይ ምን ያህል ጊዜ እንደፈጀ መተግበሪያው መረጃ መስጠቱ የተጠያቂነት አሰራርን በመዘርጋት ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ማስቻሉን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በማዘጋጃ ቤቱ ዲጂታል አገልግሎት የስም ዝውውር ለማድረግ፣ የይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ለማግኘት፣ የግንባታ ፈቃድ ለመውሰድ፣ ለዋስትና አገልግሎቶች እና ለማንኛውም ከመሬት ጋር ተያይዞ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ እየተሰጠ ነው ብለዋል።

በቀጣይም እንደ ባንክ፣ ፖስታ ቤት፣ ቴሌኮም፣ ኤሌክትሪክና እና ውሃ ያሉ አገልግሎቶችን ከማዕከሉ ጋር በማስተሳሰር ተገልጋዮች በአንድ ማዕከል ዘርፈ-ብዙ አገልግሎት የሚያገኙበት ሁኔታም እንደሚመቻች አስተባባሪው አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026