የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የጂንካ ከተማ ዲጂታላይዝድ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ተገልጋዮች በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን እንዲፈጽሙ አስችሏል

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ሰኔ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የጂንካ ከተማ ዲጂታላይዝድ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ተገልጋዮች በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን እንዲፈጽሙ ማስቻሉ ተገለጸ፡፡

የከተማው የአንድ ማዕከል ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በከተማዋ ቀደም ሲል በአሰራር ሲስተዋል የነበረውን ችግር በመፍታት የተገልጋዮችን እንግልት ማስቀረቱን ባለጉዳዮች ተናግረዋል።

የአገልግሎት አሰጣጡን አስመልክቶ ኢዜአ ካነጋገራቸው ተገልጋዮች መካከል አቶ ስሜነህ ካሳሁን እንደገለፁት፤ የማዘጋጃ ቤቱ የቀደመ አሰራር ኋላ ቀር በመሆኑ ተገልጋዩን ለውጣ ውረድ ሲያጋልጥ ቆይቷል።

ይህን ችግር ለመፍታት በአሁኑ ወቅት የተጀመረው የአንድ ማዕከል ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በዲጂታል ታግዞ መሰጠቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ለመፈጸም እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

ሌላኛው የማዘጋጃ ቤቱ ተገልጋይ አቶ አሊ ሙሐመድ በበኩላቸው፤ በአንድ ማዕከል ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የታዩ የአሰራር ለውጦችን ወደ ሌሎች ተቋማት ማስፋት እንደሚገባ ተናግረዋል።

አገልግሎቱ ከቢሮክራሲና ሙስና የፀዳ መሆኑ ቀደም ሲል በአገልግሎት አሰጣጥ ይስተዋል የነበረን የመልካም አስተዳደር ችግር መፍታቱንም አመልክተዋል።

የጂንካ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት የአንድ ማዕከል አስተባባሪ አቶ ተመስገን ጋናቡል በበኩላቸው፤ የማዘጋጃ ቤቱን አሰራር ለማዘመን ለሰው ሀይል ልማትና ለቴክኖሎጂ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።

ማዘጋጃ ቤቱ ቀደም ሲል በወረቀት አገልግሎቶችን ሲሰጥ በነበረባቸው ወቅቶች ፋይል ከመጥፋት ባለፈ በተገቢው ባለመደራጀት ለፍለጋ ሲወስድ የነበረን ረጅም ጊዜ ለማስቀረት ወደ ዲጂታል የምዝገባ ስርአት መግባቱን ጠቁመዋል።

በዲጂታል ቴክኖሎጂው የአንድ ተገልጋይ ጉዳይ ምን ያህል ጊዜ እንደፈጀ መተግበሪያው መረጃ መስጠቱ የተጠያቂነት አሰራርን በመዘርጋት ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ ማስቻሉን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በማዘጋጃ ቤቱ ዲጂታል አገልግሎት የስም ዝውውር ለማድረግ፣ የይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ለማግኘት፣ የግንባታ ፈቃድ ለመውሰድ፣ ለዋስትና አገልግሎቶች እና ለማንኛውም ከመሬት ጋር ተያይዞ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ እየተሰጠ ነው ብለዋል።

በቀጣይም እንደ ባንክ፣ ፖስታ ቤት፣ ቴሌኮም፣ ኤሌክትሪክና እና ውሃ ያሉ አገልግሎቶችን ከማዕከሉ ጋር በማስተሳሰር ተገልጋዮች በአንድ ማዕከል ዘርፈ-ብዙ አገልግሎት የሚያገኙበት ሁኔታም እንደሚመቻች አስተባባሪው አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

ባሕርዳር፤ ጳግሜ 5/ 2018 (ኢዜአ) ፡-የሀገርን ቀጣይ ተስፋ እና የትውልዱን እጣ ፋንታ የተሻለ ለማድረግ የዛሬው ብርታትና ትጋታችን ወሳኝ ነው ሲሉ የአማራ ...

Sep 11, 2026

በክልሉ ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት ተደርጓል

ወላይታ ሶዶ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ን...

Sep 10, 2026

በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል

ባህር ዳር፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የግብርናውን ዘርፍ ከአምራች ኢንዱስትሪው ጋር በማስተሳሰር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ...

Sep 7, 2026

በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ ነው

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 24/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ለአሳ አጥማጆች የተደረገው የግብአት ድጋፍ አበረታች ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሃ...

Aug 31, 2026