የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የዲጅታል ግብርና መስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5 / 2018 (ኢዜአ)፦የዲጅታል ግብርና አሰራር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተስፋፋ መሆኑ ምርታማነትን ለማሳደግና የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ዲጅታል ግብርና ከልማዳዊ የእርሻ አሰራር ወደ እውቀትና ቴክኖሎጂ መር ኢንዱስትሪ በመቀየር፣ ሀገራዊ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥና የግብርና ምርቶችን የውጭ ኤክስፖርት አቅም ማሳደግ የሚያስችል መፍትሄ ነው።

በተጨማሪም ዲጅታል ግብርና ማለት ምርታማነትን ለመጨመርና ፈጣን ውሳኔዎችን ለማሳለፍ እንደ ኢንተርኔት፣ ድሮን እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ያሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በግብርናው ዘርፍ ውስጥ መጠቀም ነው።

የግብርና ሚኒስቴር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ዓመታዊ የዲጂታል ግብርና ኤክስቴንሽንና የምክር አገልግሎት ፎረም አካሂዷል።


የግብርና ሚኒስትር ዴዔታ አማካሪ ፕሮፌሰር አሊ መሐመድ በዚሁ ጊዜ፤ የዘርፉ ክፍለ ኢኮኖሚ ለሥራ ዕድል፣ ለምግብ ሉዓላዊነትና እና ለውጭ ምንዛሬ ግኝት የላቀ ሚና ያለው የአገር ውስጥ የጀርባ አጥንት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ይሁን እንጂ ዘርፉ ለዘመናት በዘመናዊ አሰራር ባለመደገፉ ምክንያት፣ አገሪቱ ካላት እምቅ ሀብት አንጻር የሚገባትን ጥቅም ሳታገኝ መቆየቷ ተናግረዋል፡፡

ይህንን ችግር ለመፍታት መንግስት ዲጅታል የግብርና ስርዓትን ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን ጠቅሰው ስርዓቱ በተለይ በአርሶ አደሩና በባለሙያው መካከል የነበረውን የመረጃ ልውውጥ ክፍተት በመሙላት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቅሰዋል፡፡

አርሶ አደሮች ሬዲዮና የእጅ ስልክን በመጠቀም ስለ አየር ንብረትና ግብዓቶች መረጃ በማግኘት በመረጃ ላይ የተመሰረተ ምርታማነትን ማሳደግ መቻላቸውን ጠቅሰዋል፡፡

አርሶ አደሩን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግና ዘርፉን ለማላቅ የዲጅታል ግብርና ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡


በግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ኤክስቴንሽን መሪ ስራ አስፈጻሚ የኔነሽ ኤጉ በበኩላቸው፤ ድጅታል ግብርና የአርሶ አደሩን የቴክኖሎጅ አጠቃቀም ማሳደጉን ገልጸዋል፡፡

ቀደም ሲል የነበረው ኋላ ቀር የግብርና አሰራር ስርዓት ወደ ዘመናዊ በማሸጋገር ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ መጠን እንዲጨምር ማስቻሉንም ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026