የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የጅማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣን አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የስራ ተነሳሽነትን አሳድጓል

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ ሰኔ 8/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሚገኙ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት፣ ለማህበረሰቡ እየሰጡት ካለው ቀልጣፋና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት በተጨማሪ የአገልጋዮችን የስራ ተነሳሽነት ማሳደጋቸው ተገለጸ።

ማዕከላቱ በብቁ ባለሙያዎች መደራጀታቸውና ዘመናዊ አሰራርን መከተላቸው ለአገልጋዩም ሆነ ለተገልጋዩ ትልቅ እረፍት መሆኑ ተመላክቷል።


የሊሙ ገነት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባለሙያዎች ሪዳ ከማል እና አዳል ኃይለማርያም፤ በማዕከሉ ለህብረተሰቡ የሚሰጡት አገልግሎት የስራ ተነሳሽነት እንደጨመረላቸው ገልጸዋል።


ማዕከሉ በቴክኖሎጂ የተደራጀ በመሆኑ የአገልግሎት ፍጥነቱን ከመጨመሩ በላይ የሰራተኛውንም ሆነ የህብረተሰቡን ውድ ጊዜ መቆጠብ አስችሏል።

በተመሳሳይም የጅማ ማዕከል ባለሙያዎች አብዱልኑራ አባተማም እና ሰሚራ ሐሰን በበኩላቸው፣ ምቹ የስራ ቦታ መፈጠሩ ያለምንም የተገልጋይ ቅሬታ ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።


ሌላው በዞኑ በቅርቡ አገልግሎት በጀመረው የኦሞ ናዳ ወረዳ አሰንዳቦ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል በማገልገል ላይ የሚገኙት ማረሜ በቀለ እና አንዋር አባዲጋ፣ ለማህበረሰቡ በንቃትና በትጋት አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ምቹ የስራ ሁኔታ መኖሩ ሰራተኞች ያለመሰልቸት በቁርጠኝነት እንዲሰሩ ማድረጉን የጠቀሱት ባለሙያዎቹ፣ በዚህም ለዓመታት የህብረተሰቡ የቆየ ጥያቄ የነበረው የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ሙሉ በሙሉ መቀረፉን አስታውቀዋል።

በማዕከላቱ አገልግሎት ለማግኘት የመጡት ሙስጠፋ አብዱረህማን በበኩላቸው፣ በአካባቢያቸው እንዲህ ያለ ዘመናዊ ማዕከል መከፈቱ በእጅጉ እንዳስደሰታቸው ገልጸው፤ ገና ወደ ማዕከሉ ስገባ ከመስተንግዶው ጀምሮ የባለሙያዎቹ አቀባበልና ፍጥነት ከፍተኛ እርካታ የሚሰጥ ነው ብለዋል።


ለመንጃ ፈቃድ አገልግሎት የመጣው ጀማል አብዱረህማንም ማዕከሉ ከምንም በላይ ወደ ህብረተሰቡ የቀረበና ለዓመታት ለነበሩ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጠ መሆኑን ተናግሯል።

በጅማ ከተማ በሚገኘው ማዕከል የልደት ካርድ ለማውጣት የመጣችው የጅማ ከተማ ነዋሪ ቤተመቅደስ አምሀ፣ ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል ማግኘቷ እንዳስደሰታት ገልጻለች።


የጅማ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ምክትል ሥራ አስኪያጅ እና የቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊ ጀማል ሳሊ፣ በማዕከሉ የሚሰጠው አገልግሎት ለተገልጋዩ ብቻ ሳይሆን ለአገልጋዮችም ጭምር የእርካታ ምንጭ መሆኑን ገልጸዋል።


ህብረተሰቡ ጊዜና ገንዘቡን ቆጥቦ ፈጣን አገልግሎት አግኝቶ መመለሱና በተሰጠው አገልግሎት ረክቶ የሚሰጠው አዎንታዊ ምላሽ ለሰራተኛው ትልቅ ተነሳሽነት መፍጠሩን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026