የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በክልሉ የሌማት ትሩፋት ትግበራ የወተት ምርታማነት እንዲጨምር አስተዋጽኦ አበርክቷል - ቢሮው

Jun 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሌማት ትሩፋት የወተት ልማት ምርታማነት እንዲጨምር አስተዋጽኦ ማበርከቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።

የሌማት ትሩፋት መርሀግብር የምግብ ሉአላዊነትን የማረጋገጥና ክብርን የማስጠበቅ ዓላማ ያለው ሲሆን በተለይ በወተት፣ ሥጋ፣ እንቁላልና ማር ትርፍ ምርት በማምረት መጠቀም ላይ ያተኮረ ነው።

መርሀግብሩ የኢትዮጵያን ደካማ አምራችነት ታሪክ በመቀየር የምግብ ሉአላዊነትን ማረጋገጥና የኢኮኖሚ እድገትን የማፋጠን ግብም አለው።

መርሃ ግብሩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ በኋላም የወተት ምርታማነትን በማሳደግ ዜጎችን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እያደረገና ገበያን ለማረጋጋት አቅም እየፈጠረ መጥቷል፡፡

በጉዳዩ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር እንደገለፁት፣ በክልሉ የሌማት ትሩፋት መርሀግብር የወተት ምርታማነት ለማሳደግ፣ የእንስሳት ዝርያን ለማሻሻል፣ የመኖ አቅርቦት እንዲጠናከር እንዲሁም በእንሰሳት ጤና አጠባበቅ ላይ ውጤት አምጥቷል።

የወተት ምርታማነት ከማሳደግ ባለፈ የገበያ ትስስርና እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ላይ በመሰራቱ በክልሉ 12 የወተት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች እንዲቋቋሙ መደላድል መፈጠሩንም አቶ ኡስማን ጠቅሰዋል።


በሆሳዕና ከተማ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማሩት አቶ አዳነ አባቴ እንደገለፁት ወደዘርፉ ከገቡ ሰባት ዓመታትን ቢያስቆጥሩም በተሻለ ተጠቃሚ ሳይሆኑ ቆይተዋል።

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራን ተከትሎ መንግስት በዘርፉ የተሰማሩ ዜጎች እንዲጠቀሙ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ሥራ መስራቱ ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።

በዚህም ዝርያቸው የተሻሻሉ ጥጆችን በማግኘት የወተት ምርታማነትን እያሳደጉ ከመምጣታቸው ባለፈ ገቢያቸውም እንዲጨምር ማድረጉን ገልጸዋል።


በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ሹርሞ ዊጥቢራ ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ ዘነበች ጋርከቦ በበኩላቸው እንዳሉት በሌማት ትሩፋት መረሀ ግብር ታቅፈው የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው ላሞችን በማርባት በወተት ልማት ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

መንግስት በፈጠረው ዕድል ተጠቅመው ከዚህ ቀደም የነበሯቸውን የወተት ላሞች ዝርያ በተሻሻሉ ዝርያዎች በመተካት ምርታማነታቸውን እያሳደጉ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026