የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የእንግሊዝ መንግሥት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማዘመን ያደረገው የቴክኖሎጂ ድጋፍ የጋራ ደኅንነትን ለማረጋገጥ ያግዛል

Jun 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018(ኢዜአ)፦ የእንግሊዝ መንግሥት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማዘመን ያደረገው የቴክኖሎጂ ድጋፍ የጋራ ደኅንነትን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላ (ዶ/ር) ገለጹ።

የእንግሊዝ መንግሥት የአቪዬሽን ዘርፉን ለማዘመን ያደረገው 25 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የቴክኖሎጂ እገዛ የርክክብ መርሐ-ግብር እና ጉብኝት በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የአቪዬሽን ደኅንነት ዋና መምሪያ መከናወኑን አገልግሎቱ ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መረጃ አመልክቷል።


በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ዳረን ዌልች የተመራ ልዑክ እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድና የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት መርሐ-ግብር ላይ የአገልግሎቱ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል ሲሳይ ቶላ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ድጋፉ በኢትዮጵያና በእንግሊዝ መካከል ያለውን ትብብርና የጋራ ደኅንነትን የማረጋገጥ አጋርነት ማሳያ ነው።

መርሐ-ግብሩ በኢትዮጵያና በእንግሊዝ መካከል ያለውን ዘላቂ አጋርነት የሚያሳይ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ጠቁመው፤ የአቪዬሽን ዘርፉን ለማዘመን የተደረገው የቴክኖሎጂ ድጋፍ በትብብር ስንሰራ በጋራ ደኅንነትና በዓለም አቀፍ ትስስር አውድ የምናሳካቸውን ድሎች ያሳያል ብለዋል።

የአቪዬሽን ደኅንነት ስጋት ተለዋዋጭና በየጊዜው እያደገ የሚመጣ የዘርፉ ፈተና ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ያለውን የበላይነት አስጠብቆ ለመዝለቅ የደኅንነት ስጋቶችን አስቀድሞ በማወቅ ማስቀረት ወሳኝ ተልዕኳች ነው ያሉት ዶ/ር ሲሳይ፤ የቴክኖሎጂ ድጋፉ የመፈጸም አቅምን ያሳድጋል ሲሉ ተናግረዋል።


ኢትዮጵያና እንግሊዝ ትብብራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመው፤ በተለይ በቢሾፍቱ የሚገነባው አዲሱ የአየር ማረፊያና ሀገሪቱ እ.አ.አ በ2027 የምታስተናግደው የኮፕ-32 ጉባኤ በተለያዩ የአጋርነት ማዕቀፎች የሚገለጹ ወሳኝ ሁነቶች መሆናቸውን አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በዓመት እስከ 120 ሚልየን መንገደኞችን የሚያስተናግድ በአፍሪካ ግዙፍ የሆነ አየር ማረፊያ እየገነባች መሆኑን አመልክተው፤ ይህ ከአቪዬሽን ደኅንነት አኳያ ከፍተኛ ዝግጁነት እንደሚፈልግ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ዳረን ዌልች በበኩላቸው፤ ሁለቱ ሀገራት እስከ ዛሬ የዘለቀና ጠንካራ ወዳጅነት እንዳላቸው ጠቁመዋል።

የአቪዬሽን ዘርፉን ለማዘመን የተደረገው እገዛ ይህንኑ የሚመሰክርና የሚያጠናክር መሆኑንም አመልክተው ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ደኅንነት ዘርፍ ያላት ቁመና የሚደነቅ መሆኑንም መስክረዋል።

በየእለቱ የምታከናውኑት ተግባር የሀገሪቱንም የእኛንም ደኅንነት ስለሚያረጋግጥ አድናቆቴን መግለጽ እወዳለሁ ያሉት አምባሳደሩ የቦሌ ዓለም-አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቁልፍ የሆነ የዓለም-አቀፍ ተጓዞች መዳረሻና ማዕከል ነው፡፡ ደኅንነትን የማረጋገጥ ጉዳይ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት መሆኑ ይታወቃል ብለዋል።


በዓለም አቀፍ ደረጃ እየተከሰቱ ያሉ የበረራ ደኅንነት ስጋቶችን ለመቀነስ ዘመናዊ መሣሪያዎችን መታጠቅ መፍትሔ ስለሚሆን በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ስራ ላይ የሚውል ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለኢትዮጵያ መበርከቱንም ተናግረዋል።

የአቪዬሽን ደኅንነት ዋና መምሪያ ዳይሬክተር አስራት ቀጄላ፤ ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ደኅንነት ዘርፍ ዓለም-አቀፍ መመዘኛዎችን በብቃት በማሟላት ተጠቃሽ ሀገር መሆኗን አረጋግጠዋል።

የእንግሊዝ መንግሥት ድጋፍም በተለያየ መንገድ ሲገለጽ መቆየቱን አመልክተው፤ ለተደረገው እገዛም ምስጋና አቅርበዋል። ከእንግሊዝ መንግሥት ጋር በተለያዩ የተቋማዊ ግንባታ መስኮች ዘርፈ ብዙ ትብብሮችን ስናደርግ ቆይተናል ይህም ለኢቪዬሽንና ለዓለም-አቀፍ አየር ትራንስፖርት ዘርፍ ደኅንነት መረጋገጥ ጉልህ ሚና ወደ ሚያበረክት ስትራቴጂክ ምዕራፍ ተሸጋግሯል ሲሉም ገልጸዋል።

የአቪዬሽን ዘርፉን ለማዘመን የተደረገው ድጋፍ ዘመኑን የዋጀ የበረራ ደኅንነትን ለማከናወን ከፍተኛ ሚና እንደሚያበረክት አቶ አስራት አመልክተዋል።

በኢትዮጵያ የእንግሊዝ ኤምባሲ በኩል የተደረገው ድጋፍ ከሀገሪቱ ‹‹ሆም ኦፊስ ኢንተርናሽናል ኦፕሬሽን›› ቢሮ የተገኘ መሆኑን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለመገናኛ ብዙኃን የላከው መረጃ ጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ አቅም እየሆነ ነው

ባህር ዳር፤ ሰኔ 2/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የማዕድን ሀብት ልማት ዘርፉ በጥናትና ምርምር በመታገዙ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረና ከፍተኛ የገቢ...

Jun 10, 2026

የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ የሕዝብን ሀብት ለልማት በማዋል በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜና ገንዘቡን ሳያባክን ሃብቱን ለልማት እንዲያውል የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥ...

Jun 9, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026