የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አብዱልመጂድ ቴቡኔ በድጋሚ የአልጄሪያ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

Jan 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2016 (ኢዜአ)፦ አብዱልመጂድ ቴቡኔ የአልጄሪያ ፕሬዝዳንት ሆነው በድጋሚ ተመርጠዋል።

በአልጄሪያ ትናንት በተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የ78 ዓመቱ ፖለቲከኛ 95 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውን የአገሪቷ የምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል።

አብዴላሊ ሃሳኒ ቼሪፍ 3 በመቶ እና ዩሱፍ ኦውቺቼ 2 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውን ዘ ኢስት አፍሪካን እና አልጀዚራ ኮሚሽኑን ዋቢ አድርገው ያወጡት ዘገባ ያመለክታል።

በፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገቡ ከ24 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መካከል 48 በመቶው ብቻ ድምጽ መስጠታቸው ተገልጿል።

በምርጫው ላይ ከ800 ሺህ በላይ በተለያዩ አገራት የሚኖሩ የአልጄሪያ ዳያስፖራዎች ድምጽ ሰጥተዋል።

ውጤቱን ተከትሎ አብዱልመጂድ ቴቡኔ ለቀጣይ አምስት ዓመታት አልጄሪያን በመምራት ይቀጥላሉ።

ቴቡኔ ከእ.አ.አ 2019 አንስቶ አልጄሪያን በፕሬዝዳንት እየመሩ እንደሚገኝ የዘ ኢስት አፍሪካን ዘገባ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025