
አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2016 (ኢዜአ)፦ አብዱልመጂድ ቴቡኔ የአልጄሪያ ፕሬዝዳንት ሆነው በድጋሚ ተመርጠዋል።
በአልጄሪያ ትናንት በተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የ78 ዓመቱ ፖለቲከኛ 95 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውን የአገሪቷ የምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል።
አብዴላሊ ሃሳኒ ቼሪፍ 3 በመቶ እና ዩሱፍ ኦውቺቼ 2 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውን ዘ ኢስት አፍሪካን እና አልጀዚራ ኮሚሽኑን ዋቢ አድርገው ያወጡት ዘገባ ያመለክታል።
በፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገቡ ከ24 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መካከል 48 በመቶው ብቻ ድምጽ መስጠታቸው ተገልጿል።
በምርጫው ላይ ከ800 ሺህ በላይ በተለያዩ አገራት የሚኖሩ የአልጄሪያ ዳያስፖራዎች ድምጽ ሰጥተዋል።
ውጤቱን ተከትሎ አብዱልመጂድ ቴቡኔ ለቀጣይ አምስት ዓመታት አልጄሪያን በመምራት ይቀጥላሉ።
ቴቡኔ ከእ.አ.አ 2019 አንስቶ አልጄሪያን በፕሬዝዳንት እየመሩ እንደሚገኝ የዘ ኢስት አፍሪካን ዘገባ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025