
አዲስ አበባ ፤ ጳጉሜን 4/2016 (ኢዜአ)፦ አብዱልመጂድ ቴቡኔ የአልጄሪያ ፕሬዝዳንት ሆነው በድጋሚ ተመርጠዋል።
በአልጄሪያ ትናንት በተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የ78 ዓመቱ ፖለቲከኛ 95 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውን የአገሪቷ የምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል።
አብዴላሊ ሃሳኒ ቼሪፍ 3 በመቶ እና ዩሱፍ ኦውቺቼ 2 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውን ዘ ኢስት አፍሪካን እና አልጀዚራ ኮሚሽኑን ዋቢ አድርገው ያወጡት ዘገባ ያመለክታል።
በፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገቡ ከ24 ሚሊዮን በላይ ዜጎች መካከል 48 በመቶው ብቻ ድምጽ መስጠታቸው ተገልጿል።
በምርጫው ላይ ከ800 ሺህ በላይ በተለያዩ አገራት የሚኖሩ የአልጄሪያ ዳያስፖራዎች ድምጽ ሰጥተዋል።
ውጤቱን ተከትሎ አብዱልመጂድ ቴቡኔ ለቀጣይ አምስት ዓመታት አልጄሪያን በመምራት ይቀጥላሉ።
ቴቡኔ ከእ.አ.አ 2019 አንስቶ አልጄሪያን በፕሬዝዳንት እየመሩ እንደሚገኝ የዘ ኢስት አፍሪካን ዘገባ ያመለክታል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026