
ሀዋሳ፤ ጥር 9/2017(ኢዜአ)፡- በጌዴኦ ዞን በተያዘው ዓመት ባለ ልዩ ጣዕም ቡና ልማትን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በዞኑ ለተያዘው ዓመት ተከላ የሚሆን ከ8 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ የቡና ዘር መዘጋጀቱ ተመላክቷል።

የጽህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ ኤርሚያስ ቸካ ለኢዜአ እንደገለጹት የባለ ልዩ ጣዕም የቡና ዘር የተዘጋጀው በዞኑ ይርጋጨፌና ገደብ ወረዳዎች በሚገኙ ሁለት ማህበራት በኩል ነው።
አምና ለጌዴኦ ዞን ብቻ የዋለ 3ሺህ 400 ኪሎ ግራም ዘር ተዘጋጅቶ በዞኑ ለሚገኙ ቡና አምራች ወረዳዎች መሰራጨቱን አስታውሰዋል።
ዘንድሮም ባለ ልዩ ጣዕም ቡና ልማትን ለማስፋፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ በዚህም በተመረጡ ሞዴል አርሶ አደሮች 8ሺህ 200 ኪሎ ግራም የባለ ልዩ ጣዕም ቡና ዘር መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
ዘንድሮ የተዘጋጀው የቡና ዘር ከዞኑ ባለፈ ለሌሎች ዞኖች እንደሚሰራጭ ተናግረዋል።
በዞኑ የይርጋጨፌ ባለ ልዩ ጣዕም ቡና ጣዕሙን ይዞ እንዲቀጥል ለማድረግ ከእንክብካቤ ጀምሮ ያረጀ ቡናን በመጎንደል የማደስ፣ ነቅሎ የመተካትና በተጨማሪ አዲስ ማሳ የመትከል ሥራ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ኤርሚያስ አስረድተዋል።

በቡና ልማት ሞዴል የሆኑትና በይርጋጨፌ ወረዳ ቆንጋ ቀበሌ የሚኖሩት አርሶ አደር ዳንኤል ደምሴ እንዳሉት ባላቸው 2 ነጥብ 8 ሄክታር የቡና ማሳ ላይ የይርጋ ጨፌንባለ ልዩ ጣዕም ቡና ያመርታሉ።
ለቡና ማሳቸው በሚያደርጉት እንክብካቤ የሚያገኙት የምርት መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።
ቀደም ባሉት ዓመታት የቡና ዘር በተናጠል ይዘጋጅ እንደነበር አስታውሰው፣ በተያዘው ዓመት በኩታ ገጠም በማህበር ተደራጅተው ያዘጋጁትን ዘር ለዞኑ ማስረከባቸውን ገልጸዋል።

ሌላው ሞዴል አርሶ አደር ሙሉጌታ ከበደ እንዳሉት ያላቸውን 6 ነጥብ 8 ሄክታር የቡና ማሳ በአግባቡ በመንከባከብ የሚያገኙትን ምርትና ገቢ እያደገ መጥቷል።
በየዓመቱ በኩታ ገጠም ማሳቸው ያረጀውን ቡና በመጎንደል፣ የማደስና በአዲስ የመተካት ስራ በመስራታቸው ምርታማነታቸው መጨመሩን ገልጸዋል።
አምና ከቡና ንግድ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ገቢ አግኝተው እንደነበር ያስታወሱት አርሶ አደሩ፣ ዘንደሮ እስከ ሦስት ሚሊዮን ብር አገኛለሁ ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።
ለዘር አቅርቦት ማህበሩ የሚያስገቡት 6 ኩንታል ዘር ማዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል።

በይርጋጨፌ ወረዳ ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት የቡና አግሮኖሚስትና ኤክስቴንሽን ኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ ጋሻው ስሜ እንዳሉት፣ በወረዳው ከሚገኙ 26 ቀበሌዎች 24ቱ ባለ ልዩ ጣዕም ቡና አምራች ናቸው።
በእነዚህ ቀበሌዎች በአጠቃላይ 20ሺህ 980 ሄክታር መሬት በቡና መሸፈኑን ገልጸው፣ በሄክታር በአማካይ 10 ነጥብ 8 ኩንታል ምርት ይገኛል ብለዋል።
በወረዳው 70 ሞዴል አርሶ አደሮችን ያቀፈ የዘር አቅርቦት ማህበር እንደሚገኝና 3ሺህ 500 ኪሎ ግራም ዘር መዘጋጀቱን አስረድተዋል።
በጌዴኦ ዞን በ135 ሺህ አባወራና እማወራ አርሶ አደሮች 76 ሺህ ሄክታር መሬት በቡና መሸፈኑን ከዞኑ ቡናና ቅመማቅመም ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025