አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮ-ቴሌኮም የኤሌክትሪክ መኪኖችን ባትሪ በፍጥነት መሙላት የሚያስችሉ ሶስት የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ይፋ አድርጓል።
ቴክኖሎጂዎቹ ተግባራዊ የሚደረጉበት የራሱ የሀይል ማስተላለፊያ ጣቢያ የተዘጋጀለት ሲሆን ይህም በአዲስ አበባ ከመገናኛ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ኢምፔራያል አካባቢ የሚገኝ ነው።
የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ቴክኖሎጂዎቹ ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን የጠበቁና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚተገበሩ ናቸው ብለዋል።
ከቴክኖሎጂዎቹ መካከል አልትራ ፋስት የተሰኘው የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ አንድ ኪሎ ሜትር መጓዝ የሚያስችል ሀይልን በአንድ ሰከንድ የሚሞላ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ሱፐር ፋስት የተሰኘው የኤሌክትሪክ ባትሪ መሙያ ቴክኖሎጂ ከ10 እስከ 30 ደቂቃ ድረስ ሙሉ ሀይል መሙላት የሚያስችል ነው ብለዋል።
ሌላኛው የሀይል ማስተላለፊያ ቴክኖሎጂ ደግሞ ድንገተኛ የሀይል መቋረጥ ሲያጋጥም በሀይል ማስተላለፊያ ጣቢያ ውስጥ ባሉ ፖሎች ላይ በተገጠሙ ቴክኖሎጂዎች አማካኝነት በቀላሉ ሀይል መስጠት የሚያስችል ስለመሆኑም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025