የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ኢትዮ-ቴሌኮም የኤሌክትሪክ መኪኖችን ባትሪ በፍጥነት መሙላት የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን ይፋ አደረገ</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮ-ቴሌኮም የኤሌክትሪክ መኪኖችን ባትሪ በፍጥነት መሙላት የሚያስችሉ ሶስት የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን ይፋ አድርጓል።

ቴክኖሎጂዎቹ ተግባራዊ የሚደረጉበት የራሱ የሀይል ማስተላለፊያ ጣቢያ የተዘጋጀለት ሲሆን ይህም በአዲስ አበባ ከመገናኛ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ኢምፔራያል አካባቢ የሚገኝ ነው።

የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ቴክኖሎጂዎቹ ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን የጠበቁና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚተገበሩ ናቸው ብለዋል።


ከቴክኖሎጂዎቹ መካከል አልትራ ፋስት የተሰኘው የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ አንድ ኪሎ ሜትር መጓዝ የሚያስችል ሀይልን በአንድ ሰከንድ የሚሞላ መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ሱፐር ፋስት የተሰኘው የኤሌክትሪክ ባትሪ መሙያ ቴክኖሎጂ ከ10 እስከ 30 ደቂቃ ድረስ ሙሉ ሀይል መሙላት የሚያስችል ነው ብለዋል።

ሌላኛው የሀይል ማስተላለፊያ ቴክኖሎጂ ደግሞ ድንገተኛ የሀይል መቋረጥ ሲያጋጥም በሀይል ማስተላለፊያ ጣቢያ ውስጥ ባሉ ፖሎች ላይ በተገጠሙ ቴክኖሎጂዎች አማካኝነት በቀላሉ ሀይል መስጠት የሚያስችል ስለመሆኑም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025