
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክቶች ላይ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቧን የኢኒሼቲቩ ፕሮጀክቶች ሰብሳቢና የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለፁ።
የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ቀጣናዊ ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በጋራ ገምግመዋል።
የኢኒሼቲቩ ሰብሳቢና የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ጉዳዩን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም ኢኒሼቲቩ በቀጣናው ሀገራት የመሰረተ ልማትና የሰው ሀብት ልማት፣ የግብርና፣ የጤና፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲሁም አደጋዎች መከላከል ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
እነዚህ የቀጣናው የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲጠናቀቁ ክትትል የሚደረግ መሆኑንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የቀጣናው የሰላምና የልማት ማዕከል በመሆኗ ኢኒሼቲቩ ውጤታማ እንዲሆን የማስተባበር ስራውን በትኩረት እየሰራች ትገኛለች ብለዋል።
ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራትን በልማት ለማስተሳሰር የየሀገራቱ የገንዘብ ሚኒስትሮች ያቋቋሙት መሆኑንም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመልማት ካላት ፍላጎት አኳያ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን እየተገበረች መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁን ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ የልማት ድጋፍ ማግኘቷን አመልክተዋል።
በተለይም በመንገድ፣ በባቡርና በሀይል መሰረተ ልማት ከጎረቤት ሀገራት ጋር ለመተሳሰር የምታደርገው ጥረት ድጋፍ እንድታገኝ አስችሏል ብለዋል።
በመጪው የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም የአፍሪካ ቀንድ የገንዘብ ሚኒስትሮችና አጋር አካላት በተገኙበት የኢኒሼቲቩ የፕሮጀክቶች አፈፃፀምና የአምስተኛ ዓመት ምስረታ መድረክ የሚካሄድ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ በዓለም ባንክ፣ በአውሮፓ ህብረትና፣ በአፍሪካ ልማት ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተመሰረተ ቀጣናዊ የትብብር ማዕቀፍ ሲሆን ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቩን ታስተባብራለች።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025