የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

<p>ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክቶች ላይ የተሻለ አፈፃፀም አሳይታለች - ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክቶች ላይ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገቧን የኢኒሼቲቩ ፕሮጀክቶች ሰብሳቢና የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለፁ።

የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ ቀጣናዊ ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በጋራ ገምግመዋል።

የኢኒሼቲቩ ሰብሳቢና የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ጉዳዩን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም ኢኒሼቲቩ በቀጣናው ሀገራት የመሰረተ ልማትና የሰው ሀብት ልማት፣ የግብርና፣ የጤና፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲሁም አደጋዎች መከላከል ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

እነዚህ የቀጣናው የልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲጠናቀቁ ክትትል የሚደረግ መሆኑንም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የቀጣናው የሰላምና የልማት ማዕከል በመሆኗ ኢኒሼቲቩ ውጤታማ እንዲሆን የማስተባበር ስራውን በትኩረት እየሰራች ትገኛለች ብለዋል።

ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራትን በልማት ለማስተሳሰር የየሀገራቱ የገንዘብ ሚኒስትሮች ያቋቋሙት መሆኑንም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመልማት ካላት ፍላጎት አኳያ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን እየተገበረች መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁን ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ የልማት ድጋፍ ማግኘቷን አመልክተዋል።

በተለይም በመንገድ፣ በባቡርና በሀይል መሰረተ ልማት ከጎረቤት ሀገራት ጋር ለመተሳሰር የምታደርገው ጥረት ድጋፍ እንድታገኝ አስችሏል ብለዋል።

በመጪው የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም የአፍሪካ ቀንድ የገንዘብ ሚኒስትሮችና አጋር አካላት በተገኙበት የኢኒሼቲቩ የፕሮጀክቶች አፈፃፀምና የአምስተኛ ዓመት ምስረታ መድረክ የሚካሄድ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ በዓለም ባንክ፣ በአውሮፓ ህብረትና፣ በአፍሪካ ልማት ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተመሰረተ ቀጣናዊ የትብብር ማዕቀፍ ሲሆን ኢትዮጵያ ኢኒሼቲቩን ታስተባብራለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026