አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ስምንት ወራት ወደ ተለያዩ ሀገራት ከላከችው ቡና ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ ከቡና 2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል።
በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት 169ሺህ ቶን ቡና በመላክ 916 ነጥብ 48 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት እቅድ ተይዞ ነበር።
ከታቀደው በላይ 257ሺህ ቶን ቡና በመላክ 1 ነጥብ 226 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ባለስልጣኑ ገልጿል።
በተገኘው ገቢ 134 በመቶ እንዲሁም በተላከው የቡና መጠን 152 በመቶ የእቅድ አፈጻጸም በማስመዝገብ የላቀ ውጤት መገኘቱን አመልክቷል።
የኢትዮጵያ የቡና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መሆኑንም በመረጃው ላይ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት 400ሺህ ቶን ቡና በመላክ 2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት ማቀዷን ከባለስልጣኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025