
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ስምንት ወራት ወደ ተለያዩ ሀገራት ከላከችው ቡና ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ ከቡና 2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል።
በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት 169ሺህ ቶን ቡና በመላክ 916 ነጥብ 48 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት እቅድ ተይዞ ነበር።
ከታቀደው በላይ 257ሺህ ቶን ቡና በመላክ 1 ነጥብ 226 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ባለስልጣኑ ገልጿል።

በተገኘው ገቢ 134 በመቶ እንዲሁም በተላከው የቡና መጠን 152 በመቶ የእቅድ አፈጻጸም በማስመዝገብ የላቀ ውጤት መገኘቱን አመልክቷል።
የኢትዮጵያ የቡና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መሆኑንም በመረጃው ላይ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት 400ሺህ ቶን ቡና በመላክ 2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት ማቀዷን ከባለስልጣኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025