
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦በአፍሪካ ግዙፉ የቴክኖሎጂ እና የጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች (ስታርትአፕ) ሁነት እንደሆነ የሚነገርለት 3ኛው ጂአይቴክስ አፍሪካ የቴክኖሎጂ መድረክ ዛሬ በሞሮኮ ማራካሽ ተጀምሯል።
መድረኩ በአፍሪካ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ ኢኖቬሽን እና የቢዝነስ ትስስር የመሪነት ስፍራ ላይ የተቀመጡ ተቋማት እና ግለሰቦችን ያገናኘ ነው።
በሁነቱ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ130 ሀገራት በላይ የተወጣጡ ከ4 ሺህ 500 በላይ ተወካዮች፣ከ1 ሺህ 400 በላይ ስራቸውን የሚያቀርቡ ኩባንያዎች እና ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ከ650 በላይ የመንግስት ተቋማት እና ከ350 በላይ ባለሀብቶች ተሳታፊ ሆነዋል።
ሳይበር ደህንነት፣ ትምህርት፣ ቴሌኮም፣ ፋይናንስ፣ ጤና፣ ስፖርት እና የግብርና ቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እና ግለሰቦች ከሚያቀርቧቸው የቴክኖሎጂ ስራ ፈጠራዎች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ።
በአህጉራዊው የቴክኖሎጂ መድረክ የማህበረሰብን ችግር የሚፈቱ እና ህይወትን የሚያቀሉ ተጨባጭ ቴክኖሎጂዎችን መፍጠር የቻሉ ኢትዮጵያውያንም ተሳታፊዎች ናቸው።
ኢትዮጵያውያኑ በሁነቱ ላይ ስራቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ዘላቂ ልማት፣ ስራ ፈጠራ እና ሌሎች ተጓዳኝ ጉዳዮች ላይ የጎንዮሽ ውይይቶች ይካሄዳሉ።
የ2025 የጂአይቴክስ አፍሪካ መድረክ ለአፍሪካ ልማት እና ዲጂታል ሽግግር ትኩረት የሚሰጥ እና አፍሪካ የዓለም የቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ስራዎች ማዕከል ለማድረግ የሚሰራ ነው።
በሞሮኮ ማራከሽ እየተካሄደ የሚገኘው መድረክም በአህጉሪቱ ያሉ ምርጥ አዕምሮዎችን በማሰባሰብ እና የእውቀት ሽግግር እንዲሳለጥ በማድረግ አፍሪካ በዓለም የቴክኖሎጂ ውድድር የመሪነቱን ቦታ እንድትይዝ አይነተኛ ሚና የሚጫወት ነው ተብሎለታል።
ዲጂታል ኢኮኖሚ ለአፍሪካ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) ከ180 ቢሊዮን ዶላር በላይ አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝ እና የአህጉሪቷ የሳይበር ደህንነት ገበያ በዓመት የ245 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል።
ጂአይቴክስ አፍሪካ እስከ ሚያዚያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የኢዜአ ሪፖርተር ከስፍራው ዘግቧል።
የቴክኖሎጂ ሁነቱ በሞሮኮ ንጉስ መሐመድ ስድስተኛ የበላይ ጠባቂነት የሚመራ ነው።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026