የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያውያን ሀሳብ አፍላቂዎች በግዙፉ የቴክኖሎጂ ሁነት ላይ ስራቸውን ያቀርባሉ

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦በአፍሪካ ግዙፉ የቴክኖሎጂ እና የጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች (ስታርትአፕ) ሁነት እንደሆነ የሚነገርለት 3ኛው ጂአይቴክስ አፍሪካ የቴክኖሎጂ መድረክ ዛሬ በሞሮኮ ማራካሽ ተጀምሯል።

መድረኩ በአፍሪካ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ ኢኖቬሽን እና የቢዝነስ ትስስር የመሪነት ስፍራ ላይ የተቀመጡ ተቋማት እና ግለሰቦችን ያገናኘ ነው።

በሁነቱ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ130 ሀገራት በላይ የተወጣጡ ከ4 ሺህ 500 በላይ ተወካዮች፣ከ1 ሺህ 400 በላይ ስራቸውን የሚያቀርቡ ኩባንያዎች እና ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ከ650 በላይ የመንግስት ተቋማት እና ከ350 በላይ ባለሀብቶች ተሳታፊ ሆነዋል።

ሳይበር ደህንነት፣ ትምህርት፣ ቴሌኮም፣ ፋይናንስ፣ ጤና፣ ስፖርት እና የግብርና ቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እና ግለሰቦች ከሚያቀርቧቸው የቴክኖሎጂ ስራ ፈጠራዎች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ።

በአህጉራዊው የቴክኖሎጂ መድረክ የማህበረሰብን ችግር የሚፈቱ እና ህይወትን የሚያቀሉ ተጨባጭ ቴክኖሎጂዎችን መፍጠር የቻሉ ኢትዮጵያውያንም ተሳታፊዎች ናቸው።

ኢትዮጵያውያኑ በሁነቱ ላይ ስራቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።

ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ዘላቂ ልማት፣ ስራ ፈጠራ እና ሌሎች ተጓዳኝ ጉዳዮች ላይ የጎንዮሽ ውይይቶች ይካሄዳሉ።

የ2025 የጂአይቴክስ አፍሪካ መድረክ ለአፍሪካ ልማት እና ዲጂታል ሽግግር ትኩረት የሚሰጥ እና አፍሪካ የዓለም የቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ስራዎች ማዕከል ለማድረግ የሚሰራ ነው።

በሞሮኮ ማራከሽ እየተካሄደ የሚገኘው መድረክም በአህጉሪቱ ያሉ ምርጥ አዕምሮዎችን በማሰባሰብ እና የእውቀት ሽግግር እንዲሳለጥ በማድረግ አፍሪካ በዓለም የቴክኖሎጂ ውድድር የመሪነቱን ቦታ እንድትይዝ አይነተኛ ሚና የሚጫወት ነው ተብሎለታል።

ዲጂታል ኢኮኖሚ ለአፍሪካ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) ከ180 ቢሊዮን ዶላር በላይ አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝ እና የአህጉሪቷ የሳይበር ደህንነት ገበያ በዓመት የ245 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል።

ጂአይቴክስ አፍሪካ እስከ ሚያዚያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የኢዜአ ሪፖርተር ከስፍራው ዘግቧል።

የቴክኖሎጂ ሁነቱ በሞሮኮ ንጉስ መሐመድ ስድስተኛ የበላይ ጠባቂነት የሚመራ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025