
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦በአፍሪካ ግዙፉ የቴክኖሎጂ እና የጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች (ስታርትአፕ) ሁነት እንደሆነ የሚነገርለት 3ኛው ጂአይቴክስ አፍሪካ የቴክኖሎጂ መድረክ ዛሬ በሞሮኮ ማራካሽ ተጀምሯል።
መድረኩ በአፍሪካ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ ኢኖቬሽን እና የቢዝነስ ትስስር የመሪነት ስፍራ ላይ የተቀመጡ ተቋማት እና ግለሰቦችን ያገናኘ ነው።
በሁነቱ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ130 ሀገራት በላይ የተወጣጡ ከ4 ሺህ 500 በላይ ተወካዮች፣ከ1 ሺህ 400 በላይ ስራቸውን የሚያቀርቡ ኩባንያዎች እና ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች፣ከ650 በላይ የመንግስት ተቋማት እና ከ350 በላይ ባለሀብቶች ተሳታፊ ሆነዋል።
ሳይበር ደህንነት፣ ትምህርት፣ ቴሌኮም፣ ፋይናንስ፣ ጤና፣ ስፖርት እና የግብርና ቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እና ግለሰቦች ከሚያቀርቧቸው የቴክኖሎጂ ስራ ፈጠራዎች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ።
በአህጉራዊው የቴክኖሎጂ መድረክ የማህበረሰብን ችግር የሚፈቱ እና ህይወትን የሚያቀሉ ተጨባጭ ቴክኖሎጂዎችን መፍጠር የቻሉ ኢትዮጵያውያንም ተሳታፊዎች ናቸው።
ኢትዮጵያውያኑ በሁነቱ ላይ ስራቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ ሳይበር ደህንነት፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ዘላቂ ልማት፣ ስራ ፈጠራ እና ሌሎች ተጓዳኝ ጉዳዮች ላይ የጎንዮሽ ውይይቶች ይካሄዳሉ።
የ2025 የጂአይቴክስ አፍሪካ መድረክ ለአፍሪካ ልማት እና ዲጂታል ሽግግር ትኩረት የሚሰጥ እና አፍሪካ የዓለም የቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ስራዎች ማዕከል ለማድረግ የሚሰራ ነው።
በሞሮኮ ማራከሽ እየተካሄደ የሚገኘው መድረክም በአህጉሪቱ ያሉ ምርጥ አዕምሮዎችን በማሰባሰብ እና የእውቀት ሽግግር እንዲሳለጥ በማድረግ አፍሪካ በዓለም የቴክኖሎጂ ውድድር የመሪነቱን ቦታ እንድትይዝ አይነተኛ ሚና የሚጫወት ነው ተብሎለታል።
ዲጂታል ኢኮኖሚ ለአፍሪካ ዓመታዊ ጥቅል ምርት (ጂዲፒ) ከ180 ቢሊዮን ዶላር በላይ አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝ እና የአህጉሪቷ የሳይበር ደህንነት ገበያ በዓመት የ245 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል።
ጂአይቴክስ አፍሪካ እስከ ሚያዚያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የኢዜአ ሪፖርተር ከስፍራው ዘግቧል።
የቴክኖሎጂ ሁነቱ በሞሮኮ ንጉስ መሐመድ ስድስተኛ የበላይ ጠባቂነት የሚመራ ነው።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025