የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የቴክኖሎጂ ክህሎታቸው የዳበረ ዜጎችን መፍጠር ቀዳሚ አጀንዳ ነው-አቶ ጥላሁን ከበደ

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ሚያዚያ 7/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቴክኖሎጂ ክህሎታቸው የዳበረ ዜጎችን መፍጠር ቀዳሚ አጀንዳ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡


ክልል አቀፍ የኢትዮ-ኮደርስ ኢኒሼቲቭ አፈጻጸም ግምገማና ንቅናቄ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት፥ የቴክኖሎጂ ክህሎታቸው የዳበረ ዜጎችን መፍጠር የክልሉ ቀዳሚ አጀንዳ ሆኖ እየተሰራ ነው።


በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ትኩረት ከተሰጣቸው ብዝሃ ዘርፎች አንዱ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሆኑን አስታውሰው፥ፕሮጀክቱ የብልጽግናን ራዕይ ለማሳካት የማይተካ ሚና አለው ብለዋል።


ሀገራት እድገት ያስመዘገቡት በቴክኖሎጂ ወደፊት በመሄዳቸው መሆኑን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ኋላቀርነትና ድህነትን ማስወገድ የምንችለው በቴክኖሎጂ የዳበረ ክህሎት ያላቸውን ዜጎች መፍጠር ሲቻል ብቻ ነው ብለዋል።


ኢትዮ ኮደርስ ዜጎችን በቴክኖሎጂ ክህሎት በማበልጸግ በዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ከማድረግ ባለፈ ለሥራ ዕድል ፈጠራ በር የሚከፍት ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል።


የኮደርስ ስልጠና ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ ቢሆንም መንግስት ዜጎች ስልጠናውን በነፃ እንዲያገኙ ማመቻቸቱ ትልቅ ዕድል ነው ብለዋል።


የክልሉ የኮደርስ ስልጠና አፈጻጸም ዝቅተኛ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ዜጎች ይህን ዕድል በመጠቀም ራሳቸውን ከዘመኑ ጋር ሊያራምዱ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል፡፡


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ እንዲሁም የኢትዮ ኮደርስ ስትሪንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር አበባየሁ ታደሰ በበኩላቸው የኢትዮ ኮደርስ ኢንሼቲቭ ለነገ የሀገር ተረካቢ ትውልድ የምንፈጥርበት ልዩ ፕሮጀክት ነው ብለዋል።


በክልሉ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት እስከ 60 ሺህ ዜጎችን በኮደርስ ለማሠልጠን ታቅዶ እስካሁን ድረስ 38 ሺህ ዜጎችን ማሠልጠን እንደተቻለ ተገልጿል።


ከእነዚህም 6 ሺህ የሚሆኑት ዓለም አቀፍ የምስክር ወረቀት ማግኘታቸውን ነው የተናገሩት።


አፈጻጸሙ ዝቅተኛ መሆኑን የገለጹት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በቀጣይ የድጋፍና ክትትል ስራውን በማጠናከር ለክልሉ የተሰጠውን ዕድል አሟጦ ለመጠቀም እንደሚሰራ ገልጸው፣ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንድወጡ ጠይቀዋል።


በመድረኩ ላይ የኢትዮ ኮደርስ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫ ላይ ያተኮረ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025