አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8/2017(ኢዜአ)፦የመንግሥት አገልግሎትን የሚያዘምኑና የሚያቀላጥፉ የዲጂታል ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም በተገመገመበት መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፥ የለውጡ መንግስት የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታን ጨምሮ በርካታ የሪፎርም ስራዎችን ተግብሯል ብለዋል።
የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑን ጠቅሰው፥ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና የዲጅታል ክህሎትና ልህቀትን በመፍጠር ለአካታች ልማት ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዲጂታል ልማት ያመጣችው ለውጥ በዓለም አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መመዘኛ የተሻለ ደረጃ ላይ እንድትገኝ አድርጓታል ነው ያሉት።
ሀገራዊ የመረጃ ቋት በማዘጋጀት የተሻለ የመረጃ ልውውጥ ለመፍጠር የተጀመሩ ተግባራትን የማፋጠን ሥራ ይከናወናል ብለዋል።
መንግሥት ከአገልግሎት አሰጣጥ አንፃር የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ለዲጂታላይዜሽን ትልቅ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰው፥ አገልግሎትን ቀልጣፋ የማድረግ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አንስተዋል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በረከት ፍስሃፅዮን በበኩላቸው፥ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።
የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣የኤክስፖርትና የውጭ ምንዛሬ ግኝት እንዲሁም የመንግስት ገቢን ከማሳደግ አንፃር ትላልቅ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መንግሥት በወሰዳቸው እርምጃዎች የዋጋ ንረትን በማረጋጋት ረገድ አበረታች ውጤት መምጣቱን ጠቅሰዋል።
ዲጂታላይዜሽንን በሁሉም ዘርፎች እውን የማድረግ ሥራዎች ውጤታማና ተጠናክረው መቀጠል ያለባቸው ናቸው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025