
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 8/2017(ኢዜአ)፦የመንግሥት አገልግሎትን የሚያዘምኑና የሚያቀላጥፉ የዲጂታል ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም በተገመገመበት መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፥ የለውጡ መንግስት የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታን ጨምሮ በርካታ የሪፎርም ስራዎችን ተግብሯል ብለዋል።

የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እየተፋጠነ መሆኑን ጠቅሰው፥ የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና የዲጅታል ክህሎትና ልህቀትን በመፍጠር ለአካታች ልማት ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዲጂታል ልማት ያመጣችው ለውጥ በዓለም አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መመዘኛ የተሻለ ደረጃ ላይ እንድትገኝ አድርጓታል ነው ያሉት።
ሀገራዊ የመረጃ ቋት በማዘጋጀት የተሻለ የመረጃ ልውውጥ ለመፍጠር የተጀመሩ ተግባራትን የማፋጠን ሥራ ይከናወናል ብለዋል።
መንግሥት ከአገልግሎት አሰጣጥ አንፃር የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ለዲጂታላይዜሽን ትልቅ ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰው፥ አገልግሎትን ቀልጣፋ የማድረግ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አንስተዋል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በረከት ፍስሃፅዮን በበኩላቸው፥ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።
የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣የኤክስፖርትና የውጭ ምንዛሬ ግኝት እንዲሁም የመንግስት ገቢን ከማሳደግ አንፃር ትላልቅ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መንግሥት በወሰዳቸው እርምጃዎች የዋጋ ንረትን በማረጋጋት ረገድ አበረታች ውጤት መምጣቱን ጠቅሰዋል።
ዲጂታላይዜሽንን በሁሉም ዘርፎች እውን የማድረግ ሥራዎች ውጤታማና ተጠናክረው መቀጠል ያለባቸው ናቸው ብለዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026