የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በሀረሪ ክልል ለካፒታል ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል - አቶ ኦርዲን በድሪ

Apr 21, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሚያዝያ 11/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ለካፒታል ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።

ርዕሰ-መስተዳድሩ በክልሉ በግንባታ ላይ የሚገኙ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እየጎበኙ ነው።

በጉብኝቱ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በክልሉ የካፒታል ፕሮጀክቶችን በልዩ ትኩረት የመፈጸም እንቅስቃሴ በቅንጅት እየተከናወነ ነው።

ፕሮጀክቶቹ የህዝቡን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የሚከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ከፍጻሜ ለማድረስም በጥራት፣ በፍጥነትና በኃላፊነት እንዲሰራም አስገንዝበዋል።


በዛሬው ዕለትም ከካቢኔያቸውና ከክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር በመሆን የሚጎበኟቸው በክልሉ ከተማና ገጠር ወረዳዎች በበጀት ዓመቱ 9 ወራት እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ነው።

በጉብኝቱም ትምህርት ቤቶች፣ የመንገድ ግንባታ፣ በከተማና ገጠር የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች ምልከታ ይካሄድባቸዋል።

እንዲሁም የገበያ ሼድ ግንባታ፣ በግል የሚከናወኑ የኢንቨስትመንት ግንባታዎች፣ የአባድር ፕላዛ የኮሪደር ልማት ግንባታና ሌሎችም እንደሚገኙባቸው ተጠቅሷል።

በተጨማሪም በ3ኛው ዙር የጀጎል ኮሪደር ልማት መርሃ-ግብር እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶች ጉብኝት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

በጉብኝቱም የክልሉ ካቢኔ አባላትና የሴክተር መስሪያ ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025