
ሐረር፤ ሚያዝያ 11/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ለካፒታል ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
ርዕሰ-መስተዳድሩ በክልሉ በግንባታ ላይ የሚገኙ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እየጎበኙ ነው።
በጉብኝቱ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በክልሉ የካፒታል ፕሮጀክቶችን በልዩ ትኩረት የመፈጸም እንቅስቃሴ በቅንጅት እየተከናወነ ነው።
ፕሮጀክቶቹ የህዝቡን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የሚከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ከፍጻሜ ለማድረስም በጥራት፣ በፍጥነትና በኃላፊነት እንዲሰራም አስገንዝበዋል።

በዛሬው ዕለትም ከካቢኔያቸውና ከክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር በመሆን የሚጎበኟቸው በክልሉ ከተማና ገጠር ወረዳዎች በበጀት ዓመቱ 9 ወራት እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ነው።
በጉብኝቱም ትምህርት ቤቶች፣ የመንገድ ግንባታ፣ በከተማና ገጠር የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች ምልከታ ይካሄድባቸዋል።
እንዲሁም የገበያ ሼድ ግንባታ፣ በግል የሚከናወኑ የኢንቨስትመንት ግንባታዎች፣ የአባድር ፕላዛ የኮሪደር ልማት ግንባታና ሌሎችም እንደሚገኙባቸው ተጠቅሷል።
በተጨማሪም በ3ኛው ዙር የጀጎል ኮሪደር ልማት መርሃ-ግብር እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶች ጉብኝት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
በጉብኝቱም የክልሉ ካቢኔ አባላትና የሴክተር መስሪያ ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026