
ሐረር፤ ሚያዝያ 11/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ለካፒታል ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
ርዕሰ-መስተዳድሩ በክልሉ በግንባታ ላይ የሚገኙ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እየጎበኙ ነው።
በጉብኝቱ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በክልሉ የካፒታል ፕሮጀክቶችን በልዩ ትኩረት የመፈጸም እንቅስቃሴ በቅንጅት እየተከናወነ ነው።
ፕሮጀክቶቹ የህዝቡን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የሚከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ከፍጻሜ ለማድረስም በጥራት፣ በፍጥነትና በኃላፊነት እንዲሰራም አስገንዝበዋል።

በዛሬው ዕለትም ከካቢኔያቸውና ከክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር በመሆን የሚጎበኟቸው በክልሉ ከተማና ገጠር ወረዳዎች በበጀት ዓመቱ 9 ወራት እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ነው።
በጉብኝቱም ትምህርት ቤቶች፣ የመንገድ ግንባታ፣ በከተማና ገጠር የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች ምልከታ ይካሄድባቸዋል።
እንዲሁም የገበያ ሼድ ግንባታ፣ በግል የሚከናወኑ የኢንቨስትመንት ግንባታዎች፣ የአባድር ፕላዛ የኮሪደር ልማት ግንባታና ሌሎችም እንደሚገኙባቸው ተጠቅሷል።
በተጨማሪም በ3ኛው ዙር የጀጎል ኮሪደር ልማት መርሃ-ግብር እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶች ጉብኝት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
በጉብኝቱም የክልሉ ካቢኔ አባላትና የሴክተር መስሪያ ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025