የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በሀረሪ ክልል ለካፒታል ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል - አቶ ኦርዲን በድሪ

Apr 21, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሚያዝያ 11/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ለካፒታል ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።

ርዕሰ-መስተዳድሩ በክልሉ በግንባታ ላይ የሚገኙ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እየጎበኙ ነው።

በጉብኝቱ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በክልሉ የካፒታል ፕሮጀክቶችን በልዩ ትኩረት የመፈጸም እንቅስቃሴ በቅንጅት እየተከናወነ ነው።

ፕሮጀክቶቹ የህዝቡን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የሚከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ከፍጻሜ ለማድረስም በጥራት፣ በፍጥነትና በኃላፊነት እንዲሰራም አስገንዝበዋል።


በዛሬው ዕለትም ከካቢኔያቸውና ከክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር በመሆን የሚጎበኟቸው በክልሉ ከተማና ገጠር ወረዳዎች በበጀት ዓመቱ 9 ወራት እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ነው።

በጉብኝቱም ትምህርት ቤቶች፣ የመንገድ ግንባታ፣ በከተማና ገጠር የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች ምልከታ ይካሄድባቸዋል።

እንዲሁም የገበያ ሼድ ግንባታ፣ በግል የሚከናወኑ የኢንቨስትመንት ግንባታዎች፣ የአባድር ፕላዛ የኮሪደር ልማት ግንባታና ሌሎችም እንደሚገኙባቸው ተጠቅሷል።

በተጨማሪም በ3ኛው ዙር የጀጎል ኮሪደር ልማት መርሃ-ግብር እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶች ጉብኝት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

በጉብኝቱም የክልሉ ካቢኔ አባላትና የሴክተር መስሪያ ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026