የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መስክ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ልማቶች ተከናውነዋል

Apr 22, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሚያዝያ 14/2017(ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መስክ የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።

የክልሉ የአስፈፃሚ እና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ዘርፎች የበጀት ዓመቱ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም እየተገመገመ ነው።


የግምገማውን መድረክ እየመሩ የሚገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እንዳሉት፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የገጠርና የከተማ ነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ልማቶች ተከናውነዋል።

በማህበራዊ፣ በምጣኔ ሃብት እና በመልካም አስተዳደር መስኮች የተከናወኑ ስራዎች የክልሉን ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ሃብቶች በላቀ ደረጃ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማስቻሉን በመጥቀስ።

እነዚህን ውጤቶች ይበልጥ ለማስቀጠል የግምገማው መድረክ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም በግምገማው የተንጠባጠቡ ስራዎችና ክፍተቶች ተለይተው እስከ ሰኔ 30 ድረስ በተቀናጀ መንገድ ለማጠናቀቅ መደላድል ይፈጠራል ብለዋል።


በግምግማው መድረክ ላይ የክልሉ የፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኢብሳ ኢብራሂም የዘጠኝ ወራት የካፒታል ፕሮጀክቶች የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በማቅረብ ላይ ናቸው።

ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ግምገማ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የየወረዳ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025