የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መስክ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ልማቶች ተከናውነዋል

Apr 22, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሚያዝያ 14/2017(ኢዜአ)፡- በሐረሪ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መስክ የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።

የክልሉ የአስፈፃሚ እና የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ዘርፎች የበጀት ዓመቱ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም እየተገመገመ ነው።


የግምገማውን መድረክ እየመሩ የሚገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ እንዳሉት፤ በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የገጠርና የከተማ ነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ልማቶች ተከናውነዋል።

በማህበራዊ፣ በምጣኔ ሃብት እና በመልካም አስተዳደር መስኮች የተከናወኑ ስራዎች የክልሉን ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ሃብቶች በላቀ ደረጃ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማስቻሉን በመጥቀስ።

እነዚህን ውጤቶች ይበልጥ ለማስቀጠል የግምገማው መድረክ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይም በግምገማው የተንጠባጠቡ ስራዎችና ክፍተቶች ተለይተው እስከ ሰኔ 30 ድረስ በተቀናጀ መንገድ ለማጠናቀቅ መደላድል ይፈጠራል ብለዋል።


በግምግማው መድረክ ላይ የክልሉ የፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኢብሳ ኢብራሂም የዘጠኝ ወራት የካፒታል ፕሮጀክቶች የስራ አፈፃፀም ሪፖርት በማቅረብ ላይ ናቸው።

ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ግምገማ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የየወረዳ አመራሮችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026