የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የሴቶችና ወጣቶችን አቅም የበለጠ በመጠቀም የአፍሪካን ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን ይገባል - አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

May 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 29/2017 (ኢዜአ)፦የሴቶችና ወጣቶችን አቅም የበለጠ በመጠቀም የአፍሪካን ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለፁ።

ዛሬን ጨምሮ ለሶሰት ቀናት የሚቆየው ስድስተኛው የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ሴት ሥራ ፈጣሪዎች የንግድ ትርዒትና ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በንግድ ትርዒቱ መክፈቻ ላይ እንዳሉት፣ አፍሪካ በ2063 ለማሳካት ከያዘቻቸው አጀንዳዎች አንዱ የሴቶችን እኩልነትና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው።

ለአፍሪካ ዘላቂና አስተማማኝ ዕድገት የተቀናጀና የተናበበ ስራ ወሳኝ ሚና እንዳለውም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ የኮሜሳ መስራች መሆኗን አስታውሰው፤ ለአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኑንም አመልክተዋል።

የሴቶችና ወጣቶችን አቅም የበለጠ በመጠቀም የአፍሪካን ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን እንደሚገባም ነው ያመለከቱት።

ኢትዮጵያ ያደረገችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለግሉ ዘርፍ ምቹ ሁኔታ የፈጠረና ተወዳዳሪነትን ያሳደገ ነው ብለዋል።

ኮሜሳ ለሴት ስራ ፈጣሪዎች እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የኮሜሳ አባል አገራት ሴቶች በንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና አላቸው።

የሚያጋጥማቸውን ፈተናዎች ተቋቁመው በንግድ ሥራ ውጤታማ የሆኑ ሴቶች መኖራቸውንም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ውህደት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን አመልክተው፤ በዘርፉ የሚያግጥሙ ተግዳሮቶችን ለይታ ለመፍትሄው እየሰራች ነው ብለዋል።

የበለፀገች አፍሪካን እውን ለማድረግ የኮሜሳ አባል አገራት የበለጠ ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባም አመልክተዋል።

በንግድ ትርዒትና ባዛሩ ላይ ከ200 በላይ የኮሜሳ አባል አገራት ሴት ስራ ፈጣሪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025