
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 29/2017 (ኢዜአ)፦የሴቶችና ወጣቶችን አቅም የበለጠ በመጠቀም የአፍሪካን ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለፁ።
ዛሬን ጨምሮ ለሶሰት ቀናት የሚቆየው ስድስተኛው የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ሴት ሥራ ፈጣሪዎች የንግድ ትርዒትና ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በንግድ ትርዒቱ መክፈቻ ላይ እንዳሉት፣ አፍሪካ በ2063 ለማሳካት ከያዘቻቸው አጀንዳዎች አንዱ የሴቶችን እኩልነትና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው።
ለአፍሪካ ዘላቂና አስተማማኝ ዕድገት የተቀናጀና የተናበበ ስራ ወሳኝ ሚና እንዳለውም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ የኮሜሳ መስራች መሆኗን አስታውሰው፤ ለአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኑንም አመልክተዋል።
የሴቶችና ወጣቶችን አቅም የበለጠ በመጠቀም የአፍሪካን ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን እንደሚገባም ነው ያመለከቱት።
ኢትዮጵያ ያደረገችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለግሉ ዘርፍ ምቹ ሁኔታ የፈጠረና ተወዳዳሪነትን ያሳደገ ነው ብለዋል።
ኮሜሳ ለሴት ስራ ፈጣሪዎች እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የኮሜሳ አባል አገራት ሴቶች በንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና አላቸው።
የሚያጋጥማቸውን ፈተናዎች ተቋቁመው በንግድ ሥራ ውጤታማ የሆኑ ሴቶች መኖራቸውንም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ውህደት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን አመልክተው፤ በዘርፉ የሚያግጥሙ ተግዳሮቶችን ለይታ ለመፍትሄው እየሰራች ነው ብለዋል።
የበለፀገች አፍሪካን እውን ለማድረግ የኮሜሳ አባል አገራት የበለጠ ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባም አመልክተዋል።
በንግድ ትርዒትና ባዛሩ ላይ ከ200 በላይ የኮሜሳ አባል አገራት ሴት ስራ ፈጣሪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን አቅርበዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026