የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የሴቶችና ወጣቶችን አቅም የበለጠ በመጠቀም የአፍሪካን ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን ይገባል - አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

May 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 29/2017 (ኢዜአ)፦የሴቶችና ወጣቶችን አቅም የበለጠ በመጠቀም የአፍሪካን ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለፁ።

ዛሬን ጨምሮ ለሶሰት ቀናት የሚቆየው ስድስተኛው የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ሴት ሥራ ፈጣሪዎች የንግድ ትርዒትና ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በንግድ ትርዒቱ መክፈቻ ላይ እንዳሉት፣ አፍሪካ በ2063 ለማሳካት ከያዘቻቸው አጀንዳዎች አንዱ የሴቶችን እኩልነትና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው።

ለአፍሪካ ዘላቂና አስተማማኝ ዕድገት የተቀናጀና የተናበበ ስራ ወሳኝ ሚና እንዳለውም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ የኮሜሳ መስራች መሆኗን አስታውሰው፤ ለአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኑንም አመልክተዋል።

የሴቶችና ወጣቶችን አቅም የበለጠ በመጠቀም የአፍሪካን ትራንስፎርሜሽን ማፋጠን እንደሚገባም ነው ያመለከቱት።

ኢትዮጵያ ያደረገችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለግሉ ዘርፍ ምቹ ሁኔታ የፈጠረና ተወዳዳሪነትን ያሳደገ ነው ብለዋል።

ኮሜሳ ለሴት ስራ ፈጣሪዎች እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የኮሜሳ አባል አገራት ሴቶች በንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና አላቸው።

የሚያጋጥማቸውን ፈተናዎች ተቋቁመው በንግድ ሥራ ውጤታማ የሆኑ ሴቶች መኖራቸውንም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ውህደት በቁርጠኝነት እየሰራች መሆኑን አመልክተው፤ በዘርፉ የሚያግጥሙ ተግዳሮቶችን ለይታ ለመፍትሄው እየሰራች ነው ብለዋል።

የበለፀገች አፍሪካን እውን ለማድረግ የኮሜሳ አባል አገራት የበለጠ ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባም አመልክተዋል።

በንግድ ትርዒትና ባዛሩ ላይ ከ200 በላይ የኮሜሳ አባል አገራት ሴት ስራ ፈጣሪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025