
ባህርዳር፤ ግንቦት 3/2017(ኢዜአ)፦ የባህር ዳር የኮሪደር ልማት ለከተማዋ መስህብነት ተደማሪ ኃብት እና ጸጋ ሆኗል ሲሉ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።
የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነው የስማርት ፖል ተከላ መጠናቀቅን ተከትሎ የመብራት አገልግሎቱን አስጀምረዋል።
አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት የባህርዳር ከተማን በማዘመን ለጎብኚዎች ለነዋሪዎችና ለኢንቨስትመንት የተመቸች ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በዚህም በከተማዋ የሶስት ኪሎ ሜትር የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የአስፋልት፣ የእግረኛና የሳይክል መንገዶችን አሟልቶ መገንባቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የአረንጓዴ ልማት፣ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ ዜጎች ተቀምጠው ጣናን የሚያዩበት መቀመጫዎችንና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን አሟልቶ የተገነባ መሆኑን ተናግረዋል።
ከተማዋን በምሽት ይበልጥ ውብና ማራኪ ለማድረግ የስማርት ፖሎችን ተከላ ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ ዛሬ የመብራት አገልግሎቱ እንዲጀመር መደረጉን ተናግረዋል።

የስማርት ፖሎቹ ከስምንት በላይ የተለያየ ቀለም ያላቸውን መብራቶች የሚያበሩ መሆናቸው ከጣና ሃይቅና ከዘንባባዎቿ ጋር ተዳምሮ ለከተማዋ ተጨማሪ የመስህብ ጸጋ ይዞ መምጣቱን ተናግረዋል።
የስማርት ፖሎቹ ከመብራት ባሻገር ለመኪና፣ ሞባይልና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች ቻርጅ ማድረጊያ የተገጠመላቸው በመሆናቸው ቴክኖሎጂዎችን በቀላሉ መጠቀም የሚያስችል ነው ብለዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026