
ባህርዳር፤ ግንቦት 3/2017(ኢዜአ)፦ የባህር ዳር የኮሪደር ልማት ለከተማዋ መስህብነት ተደማሪ ኃብት እና ጸጋ ሆኗል ሲሉ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።
የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነው የስማርት ፖል ተከላ መጠናቀቅን ተከትሎ የመብራት አገልግሎቱን አስጀምረዋል።
አቶ ጎሹ እንዳላማው እንደገለጹት የባህርዳር ከተማን በማዘመን ለጎብኚዎች ለነዋሪዎችና ለኢንቨስትመንት የተመቸች ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በዚህም በከተማዋ የሶስት ኪሎ ሜትር የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የአስፋልት፣ የእግረኛና የሳይክል መንገዶችን አሟልቶ መገንባቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የአረንጓዴ ልማት፣ የመዝናኛ ስፍራዎች፣ ዜጎች ተቀምጠው ጣናን የሚያዩበት መቀመጫዎችንና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን አሟልቶ የተገነባ መሆኑን ተናግረዋል።
ከተማዋን በምሽት ይበልጥ ውብና ማራኪ ለማድረግ የስማርት ፖሎችን ተከላ ሙሉ በሙሉ በማጠናቀቅ ዛሬ የመብራት አገልግሎቱ እንዲጀመር መደረጉን ተናግረዋል።

የስማርት ፖሎቹ ከስምንት በላይ የተለያየ ቀለም ያላቸውን መብራቶች የሚያበሩ መሆናቸው ከጣና ሃይቅና ከዘንባባዎቿ ጋር ተዳምሮ ለከተማዋ ተጨማሪ የመስህብ ጸጋ ይዞ መምጣቱን ተናግረዋል።
የስማርት ፖሎቹ ከመብራት ባሻገር ለመኪና፣ ሞባይልና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች ቻርጅ ማድረጊያ የተገጠመላቸው በመሆናቸው ቴክኖሎጂዎችን በቀላሉ መጠቀም የሚያስችል ነው ብለዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025