አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦የኮንስትራክሽን ዘርፉ በኢትዮጵያ ስራ እድል ፈጠራ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።
20ኛው የዓለም ሥራ ድርጅት በሥራ ላይ የተመሰረተ የባለሙያዎች አህጉራዊ ስብሰባ "የማይበገር ማህበረሰብ እና ጤናማ አካባቢ የሰው ኃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም አካሄዶች" በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።
በስብሰባው የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት ተወካዮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።
ከስብሰባው ጎን ለጎንም ሀገራት በሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ያላቸውን ተሞክሮ የሚለዋወጡበት የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
በሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ የተካሄደውን ውይይት የመሩት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለስራ እድል ፈጠራ ቁርጠኛ ሆኖ እየሰራ ነው።
በተለያዩ ዘርፎች የስራ እድል ለመፍጠር ፖሊሲዎችና መርሃ ግብሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑንም አብራርተዋል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት እና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ለሥራ ዕድል ፈጠራ ያላቸውን አቅም በመገንዘብ ትኩረት መደረጉንም ገልፀዋል።
በተለይ መንግስት በስፋት እያከናወነ ያለው የመሠረተ ልማት ዝርጋታ እንደ መንገድ እና ሌሎች ግዙፍ የልማት አውታሮች በኮንስትራክሽን ዘርፍ ከፍተኛ የሥራ ዕድል እየፈጠሩ ነው ብለዋል።
ለአብነትም በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች በሥራ ዕድል ፈጠራ አይተኬ ሚና እየተጫወቱ እንዳሉ አንስተዋል።
የኮንስትራክሽን ዘርፉ ለሀገር ዕድገት ከሚያበረክተው አስተዋፅኦ ባሻገር በስራ ዕድል ፈጠራ ድርሻው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።
ዘርፉም በኢትዮጵያ እያደገ መሆኑን ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታ ማረጋገጥ እንደሚችሉም አንስተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025