
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2017(ኢዜአ)፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በጎንደር ከተማ በከፊል የተጣራ የአኩሪ አተር ዘይት የሚያመርተውን የቲቲኬ ኢንደስትሪን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ለመጎብኘት ጎንደር ከተማ ገብተዋል።
ጎንደር አፄ ቴዎድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የከተማዋ ህዝብ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ በከፊል የተጣራ የአኩሪ አተር ዘይት የሚያመርተውን የቲቲኬ ኢንደስትሪን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።
ኢንደስትሪው በ374 ሚሊዮን ብር የተገነባ ሲሆን በቀን 120 ቶን የአኩሪ አተር ዱቄት እና በከፊል የተጣራ የምግብ ዘይት የማምረት አቅም እንዳለውም ተገልጿል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቲቲኬ ኢንደስትሪ ፋብሪካ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለጀመርነው የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት አንድ ሁነኛ አብነት ነው ብለዋል።
ጎንደር ሰላምን በማስጠበቅና በማጽናት ልማትን የማረጋገጥ ለዕድገትም የመትጋት ደማቅ ማሳያ እንደሆነች ተናግረዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026