
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2017(ኢዜአ)፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በጎንደር ከተማ በከፊል የተጣራ የአኩሪ አተር ዘይት የሚያመርተውን የቲቲኬ ኢንደስትሪን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ለመጎብኘት ጎንደር ከተማ ገብተዋል።
ጎንደር አፄ ቴዎድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የከተማዋ ህዝብ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ በከፊል የተጣራ የአኩሪ አተር ዘይት የሚያመርተውን የቲቲኬ ኢንደስትሪን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።
ኢንደስትሪው በ374 ሚሊዮን ብር የተገነባ ሲሆን በቀን 120 ቶን የአኩሪ አተር ዱቄት እና በከፊል የተጣራ የምግብ ዘይት የማምረት አቅም እንዳለውም ተገልጿል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቲቲኬ ኢንደስትሪ ፋብሪካ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለጀመርነው የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት አንድ ሁነኛ አብነት ነው ብለዋል።
ጎንደር ሰላምን በማስጠበቅና በማጽናት ልማትን የማረጋገጥ ለዕድገትም የመትጋት ደማቅ ማሳያ እንደሆነች ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025