የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያና ስሎቪኒያ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና ህዋ ሳይንስ በትብብር እንደሚሰሩ ገለጹ

Jun 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና ስሎቪኒያ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና በህዋ ሳይንስ በትብብር እንደሚሰሩ ገለጹ።

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የስሎቪኒያ ፕሬዚዳንት ናታሻ ፒርክ ሙሳርን በብሔራዊ ቤተመንግስት ተቀብለው አነጋግረዋል።

ፕሬዚዳንት ታዬ ከውይይቱ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ከስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጋር በዓለም አቀፍና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል።

ስሎቪኒያ የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል በመሆኗ በቆይታዋ፣ ምክር ቤቱ የአፍሪካ ጉዳዮችን በሚያይበት ወቅት ማገዝ በምትችልባቸው ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል።

አፍሪካን በሚመለከት ሚዛናዊ እይታ ያላቸው፣ የአፍሪካ ድምጽ በመታበይ ስሜት ሳይሆን እኩልነትና ሚዛናዊነትን የሚፈልጉ እንደሆኑ መረዳታቸውን አንስተዋል።

የጸጥታው ምክር ቤት በጂኦ-ፖለቲካልና ጂኦ-ኢኮኖሚክ መስፈርቶችና የአገራት ብሔራዊ ጥቅምን ማዕከል በማድረግ ሪፎርም ለማድረግ መሰራት ባለባቸው ጉዳዮች ዙሪያም መወያየታቸውን ተናግረዋል።

ዓለም አቀፍ ውጥረት የባለብዙወገን ሃሳብና ዲፕሎማሲ ፈተና ውስጥ ከወደቀባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ እንደሆነ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጠቁመዋል።

ጥቂት ሀገራት በአለም ህልውና ላይ ሊወስኑ እንደማይገባ በመግለጽ በመካከለኛ ሃይል ሊፈረጁ የሚችሉ ሀገራት ሊኖራቸው በሚችለው ድምጽ ላይ መክረናል ብለዋል።

በሁለትዮሽ ጉዳዮች ስሎቪኒያ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና በስፔስ ሳይንስ ያላትን የዳበረ አቅም በማሸጋገር ዙሪያ በጋራ ለመስራት በአጽእኖት መወያየታቸውን ገልጸዋል።

በምግብ ራስን ለመቻል በከተማ ግብርና በንብ ማነብ ያላቸውን ልምድ በማካፈል በትብብር እንደሚሰሩም አብራርተዋል።

የስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ናታሻ ፒርክ ሙሳር በበኩላቸው፤ ከኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጋር በሁለትዮሽ፣ በአለም አቀፍና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ላይ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ስሎቪኒያ ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግም ገልጸዋል።

ከኢትዮጵያ ጋር በምጣኔ ሃብት፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የውሃ አስተዳደርና በሌሎች ዘርፎች በትብብር መስራት የሚፈልጉባቸው እንደሆኑ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025