የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያና ስሎቪኒያ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና ህዋ ሳይንስ በትብብር እንደሚሰሩ ገለጹ

Jun 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያና ስሎቪኒያ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና በህዋ ሳይንስ በትብብር እንደሚሰሩ ገለጹ።

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ የስሎቪኒያ ፕሬዚዳንት ናታሻ ፒርክ ሙሳርን በብሔራዊ ቤተመንግስት ተቀብለው አነጋግረዋል።

ፕሬዚዳንት ታዬ ከውይይቱ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ከስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጋር በዓለም አቀፍና የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ገልጸዋል።

ስሎቪኒያ የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል በመሆኗ በቆይታዋ፣ ምክር ቤቱ የአፍሪካ ጉዳዮችን በሚያይበት ወቅት ማገዝ በምትችልባቸው ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል።

አፍሪካን በሚመለከት ሚዛናዊ እይታ ያላቸው፣ የአፍሪካ ድምጽ በመታበይ ስሜት ሳይሆን እኩልነትና ሚዛናዊነትን የሚፈልጉ እንደሆኑ መረዳታቸውን አንስተዋል።

የጸጥታው ምክር ቤት በጂኦ-ፖለቲካልና ጂኦ-ኢኮኖሚክ መስፈርቶችና የአገራት ብሔራዊ ጥቅምን ማዕከል በማድረግ ሪፎርም ለማድረግ መሰራት ባለባቸው ጉዳዮች ዙሪያም መወያየታቸውን ተናግረዋል።

ዓለም አቀፍ ውጥረት የባለብዙወገን ሃሳብና ዲፕሎማሲ ፈተና ውስጥ ከወደቀባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ እንደሆነ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጠቁመዋል።

ጥቂት ሀገራት በአለም ህልውና ላይ ሊወስኑ እንደማይገባ በመግለጽ በመካከለኛ ሃይል ሊፈረጁ የሚችሉ ሀገራት ሊኖራቸው በሚችለው ድምጽ ላይ መክረናል ብለዋል።

በሁለትዮሽ ጉዳዮች ስሎቪኒያ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና በስፔስ ሳይንስ ያላትን የዳበረ አቅም በማሸጋገር ዙሪያ በጋራ ለመስራት በአጽእኖት መወያየታቸውን ገልጸዋል።

በምግብ ራስን ለመቻል በከተማ ግብርና በንብ ማነብ ያላቸውን ልምድ በማካፈል በትብብር እንደሚሰሩም አብራርተዋል።

የስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ናታሻ ፒርክ ሙሳር በበኩላቸው፤ ከኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ጋር በሁለትዮሽ፣ በአለም አቀፍና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ላይ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ስሎቪኒያ ሙሉ ድጋፍ እንደምታደርግም ገልጸዋል።

ከኢትዮጵያ ጋር በምጣኔ ሃብት፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የውሃ አስተዳደርና በሌሎች ዘርፎች በትብብር መስራት የሚፈልጉባቸው እንደሆኑ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026