የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ሕብረተሰቡ የባቡር መሰረተ ልማቶችን በአግባቡ በመጠቀምና በመጠበቅ ሀገራዊ ሃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል

Jun 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2017 (ኢዜአ)፦ሕብረተሰቡ የባቡር መሰረተ ልማቶችን በአግባቡ በመጠቀምና ተገቢውን ጥበቃ በማድረግ ሀገራዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ጥሪ አቀረበ።


የትራንስፖርት መሰረተ ልማቶች መሟላት ፈጣን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን በማሳለጥ ለአንድ አገር ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና ፖለቲካዊ መረጋጋት ጉልህ ሚና ይጫወታሉ።


በኢትዮጵያ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ለማሳደግና የገቢና ወጪ ንግዱን ለማሳለጥ የባቡር መሰረተ ልማቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።


ይሁንና በእነዚህ መሰረተ ልማቶች ላይ ከአጠቃቀም ጉድለትና የባለቤትነት ስሜት ማጣት ምክንያት ተደጋጋሚ ጉዳቶች ሲደርሱ ይስተዋላል።


ይህም የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎቱን በማስተጓጎል ተጠቃሚውን ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዲሁም በሀገር ሃብት ላይ ኪሳራ ያደርሳል።


የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጅነር ህሊና በላቸው ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኮርፖሬሽኑ የሚገነባቸው የባቡር መሰረተ ልማቶች ከፍተኛ የአገር ሃብት የፈሰሰባቸው ናቸው።


ኮርፖሬሽኑ ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎችን በማከናወን በራስ አቅም የመሰረተ ልማቶችን ለመገንባት ጥረት እያደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ የማማከርና የመልቲሞዳል ፍቃድ አግኝቶ አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።


ይህም የሎጂስቲክስ አገልግሎቱን የበለጠ ለማሳደግና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን ለማሳለጥ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።


በከፍተኛ ወጪ የሚገነቡት የባቡር መሰረተ ልማቶች በአግባቡ ካልተጠበቁ የታለመላቸውን የረጅም ጊዜ አገልግሎት እንደማይሰጡ አመልክተዋል።


በመሰረተ ልማቶቹ ላይ ተደጋጋሚ ጉዳት እንደሚደርስ ጠቁመው፣ሕብረተሰቡ መሰረተ ልማቶቹን በአግባቡ በመጠቀም አገራዊ ሃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።


የባቡር መሰረተ ልማቶቹ ባሉባቸው አካባቢዎች ከሕብረተሰቡ ጋር በመወያየት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እንደሚሰሩን አመልክተዋል።


ከጸጥታ አካላትና ከየአካበቢው ኮሚኒቲ ፖሊስ ጋር በመሆን የመሰረተ ልማቱ ተገቢውን ጥበቃ እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025