የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የህግ ታራሚዎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ይበልጥ ማሳደግ ይገባል

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 6/2017(ኢዜአ)፦ የህግ ታራሚዎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት ተናገሩ።

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር በመተባበር በኮሚሽኑ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ለህግ ታራሚዎች አገልግሎት የሚውል የፕላዝማ ችሎት አገልግሎትና የኢ-ፋይሊንግ ሥርዓትን አበልፅጎ ወደ ስራ አስገብቷል።


የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ማረሚያ ቤቶች የፍርድ ቤቶችን ውሳኔ የሚያስፈጽሙ በመሆናቸው ህገ-መንግስቱን፣ የኢትዮጵያንና የዓለም አቀፍ ህጎችን ባከበረ መልኩ ታራሚዎችን መያዝ ይገባቸዋል፡፡

በዚህም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ጋር በመተባበር የፕላዝማ ችሎት እና ኢ-ፋይሊንግ ሲስተም አበልፅጎ ወደ ስራ አስገብቷል ነው ያሉት።

የቀጠሮ ምልልስ፣ እንግልት እና ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም ይህን ፕሮጀክት ወደ ስራ ማስገባት አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አንስተዋል።

ተቋማትን በቴክኖሎጂ በማዘመን የታራሚዎችን የፍትህ ጥያቄ በፍጥነት መመለስ እንደሚያስችል ገልጸው፤ የህግ ታራሚዎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ይበልጥ ማሳደግ ይገባል ብለዋል።


የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ በበኩላቸው መንግስት ባስቀመጠው የሪፎርም አቅጣጫ መሠረት ማረሚያ ቤቶች ዜጎች ታርመውና ታንፀው አምራችና ህግ አክባሪ ሆነው ወደ ሠላማዊ ህይወት እንዲመለሱ አበረታች ተግባር መከናወኑን ተናግረዋል።

ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የፕላዝማ ችሎት አገልግሎት እና ኢ-ፋይሊንግ ሲስተም አንዱ ማሳያ መሆኑን በመጠቆም።

የሪፎርም ዕቅዱ ካስቀመጣቸው የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የህግ ታራሚዎችን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ማሻሻል ነው ብለዋል።

የተጀመሩ የለውጥ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ኮሚሽነር ጄኔራሉ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025