የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የህግ ታራሚዎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ይበልጥ ማሳደግ ይገባል

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 6/2017(ኢዜአ)፦ የህግ ታራሚዎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት ተናገሩ።

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር በመተባበር በኮሚሽኑ ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ለህግ ታራሚዎች አገልግሎት የሚውል የፕላዝማ ችሎት አገልግሎትና የኢ-ፋይሊንግ ሥርዓትን አበልፅጎ ወደ ስራ አስገብቷል።


የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ማረሚያ ቤቶች የፍርድ ቤቶችን ውሳኔ የሚያስፈጽሙ በመሆናቸው ህገ-መንግስቱን፣ የኢትዮጵያንና የዓለም አቀፍ ህጎችን ባከበረ መልኩ ታራሚዎችን መያዝ ይገባቸዋል፡፡

በዚህም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ጋር በመተባበር የፕላዝማ ችሎት እና ኢ-ፋይሊንግ ሲስተም አበልፅጎ ወደ ስራ አስገብቷል ነው ያሉት።

የቀጠሮ ምልልስ፣ እንግልት እና ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም ይህን ፕሮጀክት ወደ ስራ ማስገባት አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አንስተዋል።

ተቋማትን በቴክኖሎጂ በማዘመን የታራሚዎችን የፍትህ ጥያቄ በፍጥነት መመለስ እንደሚያስችል ገልጸው፤ የህግ ታራሚዎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ይበልጥ ማሳደግ ይገባል ብለዋል።


የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ በበኩላቸው መንግስት ባስቀመጠው የሪፎርም አቅጣጫ መሠረት ማረሚያ ቤቶች ዜጎች ታርመውና ታንፀው አምራችና ህግ አክባሪ ሆነው ወደ ሠላማዊ ህይወት እንዲመለሱ አበረታች ተግባር መከናወኑን ተናግረዋል።

ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የፕላዝማ ችሎት አገልግሎት እና ኢ-ፋይሊንግ ሲስተም አንዱ ማሳያ መሆኑን በመጠቆም።

የሪፎርም ዕቅዱ ካስቀመጣቸው የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የህግ ታራሚዎችን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ማሻሻል ነው ብለዋል።

የተጀመሩ የለውጥ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ኮሚሽነር ጄኔራሉ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026