የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገት እና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የላቀ ሚና አላቸው

Jun 23, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ) አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገት እና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የላቀ ሚና እንዳላቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አንተነህ ፈቃዱ ገለጹ።

ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን "የሳይንስ ኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ" በሚል መሪ ሃሳብ በወልቂጤ ከተማ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ እና ውድድር ተጠናቋል፡፡

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አንተነህ ፈቃዱ፤ አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገትና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ሚናቸው የላቀ ነው ብለዋል።


በመሆኑም የማህበረሰብ ችግሮችን መሰረት ያደረጉ የሳይንስና የፈጠራ ውጤቶችን ስኬታማ ለማድረግ ከትምህርት ተቋማትና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

በእውቀትና በክህሎት ላይ የተመሰረተ አሰራርን በማጠናከር የክልሉን ብሎም የሀገርን እድገት እውን ለማድረግ መትጋት ይኖርብናልም ብለዋል።

የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ሰላሙ አማዶ፤ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ከሀገርም የተሻገረ ፋይዳ እንዲኖራቸው ማዳበርና ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።


የክልሉ ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ኢንተርፕራይዞች አዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶችን በመቅዳትና ለማህበረሰቡ በማሸጋገር ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትልቁን ድርሻ እንደሚወስዱ ተናግረዋል፡፡


በኤግዚቢሽኑ የፈጠራ ስራቸውን ካቀረቡ ተማሪዎች መካከል በወልቂጤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው እሱባለው ተክለወልድ የግብርና ቴክኖሎጂን ለማዘመን የሚያግዝ የፈጠራ ስራ ይዞ መቅረቡን ተናግሯል።


የፈጠራ ስራው የገጠሩን ማህበረሰብ ግብርናን በማዘመን ከድህረ ምርት እስከ ምርት ሂደት በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ ክትትል ለማድረግና ምርታማነትን ለመጨመር የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጸው።

በመርሐ ግብሩ ላይ የፈጠራ ባለቤቶች፣ የክልል፣ የዞንና የልዩ ወረዳ አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላትም ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025