
ሆሳዕና ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ) አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገት እና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የላቀ ሚና እንዳላቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አንተነህ ፈቃዱ ገለጹ።
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን "የሳይንስ ኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ" በሚል መሪ ሃሳብ በወልቂጤ ከተማ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ እና ውድድር ተጠናቋል፡፡
በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አንተነህ ፈቃዱ፤ አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገትና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ሚናቸው የላቀ ነው ብለዋል።

በመሆኑም የማህበረሰብ ችግሮችን መሰረት ያደረጉ የሳይንስና የፈጠራ ውጤቶችን ስኬታማ ለማድረግ ከትምህርት ተቋማትና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
በእውቀትና በክህሎት ላይ የተመሰረተ አሰራርን በማጠናከር የክልሉን ብሎም የሀገርን እድገት እውን ለማድረግ መትጋት ይኖርብናልም ብለዋል።
የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ሰላሙ አማዶ፤ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ከሀገርም የተሻገረ ፋይዳ እንዲኖራቸው ማዳበርና ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።

የክልሉ ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ኢንተርፕራይዞች አዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶችን በመቅዳትና ለማህበረሰቡ በማሸጋገር ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትልቁን ድርሻ እንደሚወስዱ ተናግረዋል፡፡

በኤግዚቢሽኑ የፈጠራ ስራቸውን ካቀረቡ ተማሪዎች መካከል በወልቂጤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው እሱባለው ተክለወልድ የግብርና ቴክኖሎጂን ለማዘመን የሚያግዝ የፈጠራ ስራ ይዞ መቅረቡን ተናግሯል።

የፈጠራ ስራው የገጠሩን ማህበረሰብ ግብርናን በማዘመን ከድህረ ምርት እስከ ምርት ሂደት በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ ክትትል ለማድረግና ምርታማነትን ለመጨመር የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጸው።
በመርሐ ግብሩ ላይ የፈጠራ ባለቤቶች፣ የክልል፣ የዞንና የልዩ ወረዳ አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላትም ተሳትፈዋል፡፡
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026