
ሆሳዕና ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ) አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገት እና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የላቀ ሚና እንዳላቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አንተነህ ፈቃዱ ገለጹ።
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን "የሳይንስ ኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ" በሚል መሪ ሃሳብ በወልቂጤ ከተማ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ እና ውድድር ተጠናቋል፡፡
በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አንተነህ ፈቃዱ፤ አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገትና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ሚናቸው የላቀ ነው ብለዋል።

በመሆኑም የማህበረሰብ ችግሮችን መሰረት ያደረጉ የሳይንስና የፈጠራ ውጤቶችን ስኬታማ ለማድረግ ከትምህርት ተቋማትና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
በእውቀትና በክህሎት ላይ የተመሰረተ አሰራርን በማጠናከር የክልሉን ብሎም የሀገርን እድገት እውን ለማድረግ መትጋት ይኖርብናልም ብለዋል።
የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ሰላሙ አማዶ፤ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ከሀገርም የተሻገረ ፋይዳ እንዲኖራቸው ማዳበርና ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።

የክልሉ ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ኢንተርፕራይዞች አዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶችን በመቅዳትና ለማህበረሰቡ በማሸጋገር ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትልቁን ድርሻ እንደሚወስዱ ተናግረዋል፡፡

በኤግዚቢሽኑ የፈጠራ ስራቸውን ካቀረቡ ተማሪዎች መካከል በወልቂጤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው እሱባለው ተክለወልድ የግብርና ቴክኖሎጂን ለማዘመን የሚያግዝ የፈጠራ ስራ ይዞ መቅረቡን ተናግሯል።

የፈጠራ ስራው የገጠሩን ማህበረሰብ ግብርናን በማዘመን ከድህረ ምርት እስከ ምርት ሂደት በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ ክትትል ለማድረግና ምርታማነትን ለመጨመር የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጸው።
በመርሐ ግብሩ ላይ የፈጠራ ባለቤቶች፣ የክልል፣ የዞንና የልዩ ወረዳ አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላትም ተሳትፈዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025