የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገት እና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የላቀ ሚና አላቸው

Jun 23, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ) አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገት እና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የላቀ ሚና እንዳላቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አንተነህ ፈቃዱ ገለጹ።

ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን "የሳይንስ ኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ" በሚል መሪ ሃሳብ በወልቂጤ ከተማ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ እና ውድድር ተጠናቋል፡፡

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አንተነህ ፈቃዱ፤ አዳዲስ የፈጠራና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ለሀገር እድገትና የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ሚናቸው የላቀ ነው ብለዋል።


በመሆኑም የማህበረሰብ ችግሮችን መሰረት ያደረጉ የሳይንስና የፈጠራ ውጤቶችን ስኬታማ ለማድረግ ከትምህርት ተቋማትና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

በእውቀትና በክህሎት ላይ የተመሰረተ አሰራርን በማጠናከር የክልሉን ብሎም የሀገርን እድገት እውን ለማድረግ መትጋት ይኖርብናልም ብለዋል።

የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ሰላሙ አማዶ፤ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ከሀገርም የተሻገረ ፋይዳ እንዲኖራቸው ማዳበርና ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።


የክልሉ ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ ኢንተርፕራይዞች አዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶችን በመቅዳትና ለማህበረሰቡ በማሸጋገር ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትልቁን ድርሻ እንደሚወስዱ ተናግረዋል፡፡


በኤግዚቢሽኑ የፈጠራ ስራቸውን ካቀረቡ ተማሪዎች መካከል በወልቂጤ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ11ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው እሱባለው ተክለወልድ የግብርና ቴክኖሎጂን ለማዘመን የሚያግዝ የፈጠራ ስራ ይዞ መቅረቡን ተናግሯል።


የፈጠራ ስራው የገጠሩን ማህበረሰብ ግብርናን በማዘመን ከድህረ ምርት እስከ ምርት ሂደት በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ ክትትል ለማድረግና ምርታማነትን ለመጨመር የሚያስችል መሆኑን ነው የገለጸው።

በመርሐ ግብሩ ላይ የፈጠራ ባለቤቶች፣ የክልል፣ የዞንና የልዩ ወረዳ አመራሮችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላትም ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026