የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ለከተሞች አስተማማኝ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻልና የመቀየር ስራ እየተሰራ ነው - አገልግሎቱ

Jun 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 13/2017(ኢዜአ)፦ ለከተሞች አስተማማኝ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻልና የመቀየር ስራ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለጸ፡፡

ተቋሙ አገልግሎቱን በማዘመን የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለመቀነስና ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በሚያደርገው ጥረት ቅንጅታዊ አሰራር መፍጠር የሚያስችል የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎቸ ጉብኝትና የሚዲያ ፎረም አካሂዷል።

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮሰስና ጥራት ማኔጅመንት ስራ አስፈፃሚ እሱባለው ጤናው እንደገለጹት፤ የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለማስቀረት በዋነኝነት መሰረተ ልማቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው።


እንዲሁም አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ መደገፍ አንዱ መሆኑ አንስተው፤ ይህም ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑ ጠቅሰዋል።

በዚህም ካሁን ቀደም በዘርፉ የነበሩ ተግዳሮቶች እየተሻሻሉ መምጣታቸውን ጨምረው ጠቁመዋል፡፡

ተቋሙ አራት መሰረታዊ ነገሮች ላይ ያተኮረ የሪፎርም ስራ እያከናወነ መሆኑን የገለጹት አቶ እሱባለው፤ በዚህም ውጤቶች ታይተዋል ብለዋል፡፡

አሁን ላይ በበርካታ ከተሞች የኤሌክትሪክ ተደራሽነትንና የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡

የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለማስቀረት የተጀመረው ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ አሰራር ማህበረሰቡ እንዲያውቀው ለማድረግና ብልሹ አሰራሮችን ለማጋለጥ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ሚና የላቀ ነው ብለዋል።

የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ስራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር በበኩላቸው፤ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማትን ከስርቆት ለመጠበቅ የማህበረሰቡ ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

መገናኛ ብዙሃንም በማህበረሰቡ ዘንድ ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

አገልግሎቱ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ተቀራርቦ ለመስራት ጉብኝት ማዘጋጀቱንና ለስራው መሳለጥ የሚድያ ፎረም ማቋቋም ማስፈለጉን በዚሁ ወቅት ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026