
አዲስ አበባ፤ሰኔ 14/2017 (ኢዜአ)፦መንግስት በየአካባቢው ያሉ ፀጋዎችን በመለየት የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለፁ።
ከለውጡ በኃላ በቱሪዝሙ ዘርፍ ከተከናወኑ ስራዎች መካከል አንዱ የሆነው የቤኑና መንደር በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ተጎብኝቷል።

የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ሰሞኑን በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ውይይት ማካሄዳቸው የሚታወቅ ነው።ከውይይቱ በኋላ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
የዶንጋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት አመራር አቶ ለገሰ ለመንጎ፥ ከጎበኟቸው የልማት ሥራዎች መካከል የቤኑና መንደር ተአምር እንደሆነባቸው አንስተዋል።

የጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ አመራር የሆኑት ወይዘሮ ሂንዲያ ሻፊ በበኩላቸው በተመለከቱት የልማት ሥራ መደነቃቸውን ነው የገለፁት።

የዓረና ትግራይ ፓርቲ አመራር አቶ ሀፍተይ ገብረሩፋኤል በሰጡት አስተያየት የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት የተከናወኑት ተግባራት መልካም መሆናቸውን የተገነዘብንበት ጉብኝት ነው ብለዋል።

ቱሪዝም ከሰላም ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንዳለው በመጥቀስ፥ በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ አካላት ችግራቸውን በውይይት በመፍታት ለዘርፉ እድገት አበርክቶ ሊያደርጉ እንደሚገባም ነው ያነሱት።

የተለያዩ የፖለቲካ አመለካከቶች ቢኖሩም በሀገር ጉዳይ ላይ በትብብር መስራት ተገቢ ነው ያሉት የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮቹ ለዚህም በቀጣይ የእኛስ አበርክቶ ምን ሊሆን ይገባል የሚለውን የቤት ስራ የሰጠ ጉብኝት ነው ብለዋል።
እንዲህ አይነት የሀገርን እድገት የሚያልቁ ተግባራትን ለመከወን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያሳዩት ቁርጠኝነትም የሚያስመሰግናቸው መሆኑን አንስተዋል።

በእድገት ጉዞ ውስጥ አሻራቸውን ያሳረፉ ባለሙያዎችም ሀገራቸውን ለማልማት ላከናወኑት ስራ አድናቆት አለን ነው ያሉት።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026