
አዲስ አበባ፤ሰኔ 14/2017 (ኢዜአ)፦መንግስት በየአካባቢው ያሉ ፀጋዎችን በመለየት የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራት አበረታች መሆናቸውን የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለፁ።
ከለውጡ በኃላ በቱሪዝሙ ዘርፍ ከተከናወኑ ስራዎች መካከል አንዱ የሆነው የቤኑና መንደር በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ተጎብኝቷል።

የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ሰሞኑን በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ውይይት ማካሄዳቸው የሚታወቅ ነው።ከውይይቱ በኋላ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
የዶንጋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት አመራር አቶ ለገሰ ለመንጎ፥ ከጎበኟቸው የልማት ሥራዎች መካከል የቤኑና መንደር ተአምር እንደሆነባቸው አንስተዋል።

የጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ አመራር የሆኑት ወይዘሮ ሂንዲያ ሻፊ በበኩላቸው በተመለከቱት የልማት ሥራ መደነቃቸውን ነው የገለፁት።

የዓረና ትግራይ ፓርቲ አመራር አቶ ሀፍተይ ገብረሩፋኤል በሰጡት አስተያየት የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት የተከናወኑት ተግባራት መልካም መሆናቸውን የተገነዘብንበት ጉብኝት ነው ብለዋል።

ቱሪዝም ከሰላም ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንዳለው በመጥቀስ፥ በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ አካላት ችግራቸውን በውይይት በመፍታት ለዘርፉ እድገት አበርክቶ ሊያደርጉ እንደሚገባም ነው ያነሱት።

የተለያዩ የፖለቲካ አመለካከቶች ቢኖሩም በሀገር ጉዳይ ላይ በትብብር መስራት ተገቢ ነው ያሉት የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮቹ ለዚህም በቀጣይ የእኛስ አበርክቶ ምን ሊሆን ይገባል የሚለውን የቤት ስራ የሰጠ ጉብኝት ነው ብለዋል።
እንዲህ አይነት የሀገርን እድገት የሚያልቁ ተግባራትን ለመከወን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያሳዩት ቁርጠኝነትም የሚያስመሰግናቸው መሆኑን አንስተዋል።

በእድገት ጉዞ ውስጥ አሻራቸውን ያሳረፉ ባለሙያዎችም ሀገራቸውን ለማልማት ላከናወኑት ስራ አድናቆት አለን ነው ያሉት።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026