
ሐረር፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ የሐረርን ገጽታ የሚያጎለብቱና የሀዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዓለም አቀፍ ቅርስ ጀጎል የተገነቡ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ግንባታና ሌሎች ስራዎችን ተመልክተዋል።

እንዲሁም የግንባታ ስራው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የአባድር ፕላዛ የኮሪደር ልማት ስራ ጨምሮ የገበያ ማዕከላት፣ የመንገድ፣ የኢንቨስትመንትና ሌሎች እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ውጤታማና የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል።
በክልሉ የተከናወኑ የኮሪደር ልማትና ሌሎች የፕሮጀክት ግንባታዎች የከተማዋን ገጽታ የቀየሩና የህዝቡን የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች የመለሱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በተለይ በኮሪደር ልማት የተከናወነው ስራ ከተማዋን የበለጠ የቱሪስት መዳረሻነት አጉልቶ ያሳየ መሆኑንም አመላክተዋል።

በአሁኑ ወቅትም የክልሉን ገጽታ የሚያጎለብቱና የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በከተማው ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው የአባድር ፕላዛ የኮሪደር ልማት በተሻለ ጥራትና ፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።
በተጨማሪም በክልሉ የተገነቡት የገበያ ማዕከላት ህገ-ወጥና የጎዳና ላይ ንግድን በመከላከል አርሶ አደሩ ምርቱን በቀላሉ ወደ ገበያ በማውጣት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርብ የሚያስችሉ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆኑ መረባረብ ይገባል ብለዋል።
በጉብኝቱ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመርን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025