
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2017(ኢዜአ)፦ በዓለም ላይ የሚስተዋሉ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን መቋቋምና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችሉ ጠንካራ ተቋማትን መፍጠር እንደሚገባ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ገለጹ።
ኢትዮጵያ ከሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በትይዩ ያስተናገደቻቸው 10ኛው የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር እና የተመድ የአፍሪካ ቀጣናዊ ፎረም ዛሬ ተጠናቀዋል።

የመንግሥት ተቋማት ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን ተቋቁመውና በየዘመኑ እየተንከባለሉ የመጡ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በመፍታት አካታች፣ ዘላቂ ልማት የሚያመጣ ተጠያቂነትን የሚያሰፍን፣ ሰብዓዊ መብት የሚያከብር፣ የህዝቦችን ትብብር የሚያጠናክሩ ተቋማትን ለመፍጠር ያለመ ነበር።
አቶ አደም ፋራህ በማጠቃለያ መርሀ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በትይዩ የተካሄዱት ሁለቱም መድረኮች በስኬት መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።
በዓለም ላይ እየተስተዋሉ ያሉ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን መቋቋምና ቀድሞ ምላሽ መስጠት የሚችሉ ጠንካራ ተቋማትን መፍጠር ይገባል ብለዋል።
በመሆኑም ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ያለውን ውስብስብነት ከግምት ያስገቡ አዳዲስ ፈጠራዎችና ሞዴሎችን ገቢራዊ ማድረግ ይገባል ነው ያሉት።
የመንግሥት አገልግሎት በአፍሪካ ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን መፍታት የሚያስችል መሆኑን በመጥቀስ፤ በአገልግሎት ሰጪዎች ላይ የክህሎት፣ የአመራር እና የትብብር አቅምን ማጎልበት ለሀገራዊ ሽግግር ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።
የኮንፍረንሱ ዓላማ የተቋም ግንባታ ብቻ ሳይሆን ለዜጎች ግልፅና ቀልጣፋ አገልግሎት የመስጠት ሀላፊነት ጭምር መሆኑን ተናግረዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፅንሰ ሀሳብ ለዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት የመነጨ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁን ባለው ሂደት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሪፎርም ከአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 እና የተመድ 2030 ዘላቂ የልማት ግቦች ጋር የተሰናሰነ መሆኑን አንስተዋል።
ስብሰባው የመንግሥት አሰራርን በቴክኖሎጂ መደገፍ፣ የሰው ሀይል አስተዳደርንና የኢኖቬሽን አገልግሎትን ማቀላጠፍ ዘመኑ የሚጠይቀውን ተቋም ለመፍጠር ያግዛል ብለዋል።
ከዚህም ባለፈ ጠንካራ ተቋማዊ አደረጃጀት በመፍጠር ተቋማዊ ተጠያቂነትን ማስፈንና የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ልምዶች የተገኙበት መሆኑንም ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025