የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው

Jul 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።

አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ በስፔን ሲቪያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በኮንፍረንሱ እየተሳተፈ ነው።

ሚኒስትሩ በኮንፍረንሱ ባደረጉት ንግግር ከ10 አመት በፊት በአዲስ አበባ ሶስተኛው ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ መካሄዱን አስታውሰዋል።

ይሁንና በኮንፍረንሱ የጸደቀው የአዲስ አበባ የድርጊት መርሃ-ግብር የአተገባበር ተግዳሮት እንደገጠመው ጠቅሰው የሲቪያ ስምምነት ይህንን ተግዳሮት የሚሻገር መሆን እንደሚገባው አመልክተዋል።

ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመተግበር ከሚያስፈልገው ፋይናንስ ውስጥ የ4 ትሪሊዮን ዶላር እጥረት መግጠሙን አንስተዋል።

ይህ ሁኔታ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራትን ለዘርፈ-ብዙ ተግዳሮቶች ዳርጓቸዋል ነው ያሉት ሚኒስትሩ።

ለአብነትም አዳጊ ሀገራት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ ለሚመጡ ቀውሶች እና ለእዳ ጫና መጋለጣቸው አሳሳቢ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ኮርፖሬሽኖች ላይ ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ የታክስ ስርዓትን መተግበርና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጥላ ስር በየነ-መንግስታዊ የብድር አስተዳደርን በማቋቋም ዘላቂ ያልሆነ የብድር ችግሮችን መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል።

በተጨማሪም የልማት ፋይናንስ ድጋፎችና ብድሮች ሀገራት ቅድሚያ ከሚሰጣቿው ጉዳዮችና እቅዶች ጋር መጣጣም እንዳለባቸውና አዳጊ ሀገራት የሚያገኙት የፋይናንስ ድጋፍ መጨመር እንዳለበት አመልክተዋል።

በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ዘላቂ እና ተገማች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖራቸውና ቀውሶችን በተገቢው መንገድ ማስተዳደር እንዲችሉና ዓለም ዓቀፍ የልማት ፋይናንስ ስምምነቶች በተገቢው እንዲተገበሩ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ሊኖር እንደሚገባም ነው የገለጹት።

በአፍሪካ እና በአጠቃላይ አዳጊ ሀገራት በመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ የስራ ዕድል ፈጠራና የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የሚያስችል የፋይናንስ አቅርቦት በአስተማማኝ መልኩ ማቅረብ ድህነትን ለመቀነስ እና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም ሚኒስትሩ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን “ዓለም አቀፍ ትብብርን በአዲስ መልክ ማደስ” በሚል ርዕስ በሚኒስትሮች ደረጃ በተደረገው ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል።

ሁለተኛው ቀኑን የያዘው አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ልዑክ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን እየተካሄዱ ባሉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025