የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው

Jul 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ።

አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ በስፔን ሲቪያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በኮንፍረንሱ እየተሳተፈ ነው።

ሚኒስትሩ በኮንፍረንሱ ባደረጉት ንግግር ከ10 አመት በፊት በአዲስ አበባ ሶስተኛው ዓለም አቀፍ የልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ መካሄዱን አስታውሰዋል።

ይሁንና በኮንፍረንሱ የጸደቀው የአዲስ አበባ የድርጊት መርሃ-ግብር የአተገባበር ተግዳሮት እንደገጠመው ጠቅሰው የሲቪያ ስምምነት ይህንን ተግዳሮት የሚሻገር መሆን እንደሚገባው አመልክተዋል።

ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመተግበር ከሚያስፈልገው ፋይናንስ ውስጥ የ4 ትሪሊዮን ዶላር እጥረት መግጠሙን አንስተዋል።

ይህ ሁኔታ በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራትን ለዘርፈ-ብዙ ተግዳሮቶች ዳርጓቸዋል ነው ያሉት ሚኒስትሩ።

ለአብነትም አዳጊ ሀገራት ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ ለሚመጡ ቀውሶች እና ለእዳ ጫና መጋለጣቸው አሳሳቢ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ኮርፖሬሽኖች ላይ ፍትሃዊ ዓለም አቀፍ የታክስ ስርዓትን መተግበርና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጥላ ስር በየነ-መንግስታዊ የብድር አስተዳደርን በማቋቋም ዘላቂ ያልሆነ የብድር ችግሮችን መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል።

በተጨማሪም የልማት ፋይናንስ ድጋፎችና ብድሮች ሀገራት ቅድሚያ ከሚሰጣቿው ጉዳዮችና እቅዶች ጋር መጣጣም እንዳለባቸውና አዳጊ ሀገራት የሚያገኙት የፋይናንስ ድጋፍ መጨመር እንዳለበት አመልክተዋል።

በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ዘላቂ እና ተገማች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖራቸውና ቀውሶችን በተገቢው መንገድ ማስተዳደር እንዲችሉና ዓለም ዓቀፍ የልማት ፋይናንስ ስምምነቶች በተገቢው እንዲተገበሩ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ሊኖር እንደሚገባም ነው የገለጹት።

በአፍሪካ እና በአጠቃላይ አዳጊ ሀገራት በመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ የስራ ዕድል ፈጠራና የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል የሚያስችል የፋይናንስ አቅርቦት በአስተማማኝ መልኩ ማቅረብ ድህነትን ለመቀነስ እና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም ሚኒስትሩ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን “ዓለም አቀፍ ትብብርን በአዲስ መልክ ማደስ” በሚል ርዕስ በሚኒስትሮች ደረጃ በተደረገው ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ዓለም አቀፍ ትብብር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል።

ሁለተኛው ቀኑን የያዘው አራተኛው ዓለም አቀፍ የዘላቂ ልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ እስከ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ልዑክ ከኮንፍረንሱ ጎን ለጎን እየተካሄዱ ባሉ የተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026