የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በሸገር ከተማ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - አስተዳደሩ

Jul 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/2017(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ።

በከተማው በኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዛሬ ተጀምሯል።

በከተማው በበጀት ዓመቱ ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ የተገነቡ የመሰረት ልማት ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።


የከተማው ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) በምረቃ ሥነስርዓቱ እንደገለጹት የከተማዋን ልማት በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

በበጀት ዓመቱ በ17 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር 384 ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው፣ ከእነዚህ ውስጥ የ308ቱ ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ በቅተዋል ብለዋል።

ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል የመስኖና የመጠጥ ተቋማት፣ ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣቢያ፣ መንገዶች፣ ፖሊስ ጣቢያ እና የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች ግንባታን በማሳያነት ጠቅሰዋል።


የኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ ሀላፊ ጫላ ደሬ በበኩላቸው ለህብረተሰቡ የልማት ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ለመስጠት ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ በክፍለ ከተማው ህብረተሰቡን በማሳተፍ የተከናወኑ 24 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ሥራ መጠናቀቁን ተናግረዋል።

የህዝብን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸው፣ ህዝቡም ለፕሮጀክቶች ስኬታማነት እያደረገ ያለውን ተሳትፎ እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።

ከልማት ፕሮጀክቶቹ ምረቃ በተጨማሪ የከተማው ነዋሪዎችን ያሰተፈ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በከተማው ኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ ድሬ ሶኮሩ ወረዳ ዛሬ ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) እንዳሉት በክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ከ40 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ለምግብነት፣ ለደንና ለውበት የሚውሉ ችግኞች ይተከላሉ።


በተመረጡ ክፍለ ከተሞችም የአቮካዶና የአፕል ችግኞችን በመትከል በክልስተር የማልማት ስራ እንደሚከናወን ጠቁመዋል።

በችግኝ ተከላው ከተሳተፉ የኩራ ጅዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ በቀለ ያኢ እና አቶ በላቸው አበራ ችግኝ ከመትከል ባለፈ በየጊዜው በመንከባከብ ለማሳደግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ችግኝ መትከል የአየር ንብርት ለውጥን ለመቋቋምና ምርታማነትን ለማሳደግ ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ በየዓመቱ በአረንጓዴ አሻራ ልማት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል።

ዛሬ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሀግብር ችግኝ በመትከል አሻራቸውን ማኖራቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸው፣ በቀጣይም የተከሏቸውን ችግኞች በመንከባከብ ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025