የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ መለመን የለባትም፤ልጆቿ ተግተው ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jul 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ):-ኢትዮጵያ መለመን የለባትም፤ልጆቿ ተግተው ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፥ አምርታ መብላት የማትችል ሀገር ብሄራዊ ጥቅሞቿን ለማሳካት እንድምትቸገር ገልጸዋል።

ምርት ከማምረት እና ከመሸጥ ባለፈ በግብርና እሴት ሰንሰለት ውስጥ ያሉ ጉዳዮች ላይ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ ማምጣት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማምጣት ያስችላል በሚል እሳቤ ሲከናወኑ የቆዩ ስራዎች ውጤት ማስገኘታቸውን አመልክተዋል።

ባለፉት ዓመታት 27 ሚሊዮን ዜጎች በሴፍቲኔት ኢኒሼቲቭ በተረጂነት ማዕቀፍ ውስጥ እንደነበሩ አስታውሰዋል።

መንግስት ዜጎችን ከሴፍቴነት ነጻ ለማውጣት በግብርናው ንዑስ ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቷቸው ሲሰሩ ከነበሩ ጉዳዮች መካከል አንዱ እንደሆነ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በምስራቅ ሐረርጌ እና በደቡብ ሃላባ በነበራቸው ቆይታ አርሶ አደሮች ከሴፍቲኔት ተላቀው በራሳቸው አቅም ማምረት መጀመራቸውን እንደተመለከቱ አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ መለመን የለባትም ልጆቿ ተግተው ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው የሚለው እምነት ፍሬ እያፈረ መምጣቱን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት።

ዘንድሮ 23 ሚሊዮን ዜጎች ከሴፍቲኔት ተረጂነት ነጻ ወጥተዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ይህ የማንሰራራት እና ኢትዮጵያ ከጥገኝነት ለመላቀቅ የጀመረችው ስራ ትልቁ ማሳያ ነው ብለዋል።

በቀጣይ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ የጋራ ጥረት እና ርብርብ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026