የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ መለመን የለባትም፤ልጆቿ ተግተው ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jul 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ):-ኢትዮጵያ መለመን የለባትም፤ልጆቿ ተግተው ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፥ አምርታ መብላት የማትችል ሀገር ብሄራዊ ጥቅሞቿን ለማሳካት እንድምትቸገር ገልጸዋል።

ምርት ከማምረት እና ከመሸጥ ባለፈ በግብርና እሴት ሰንሰለት ውስጥ ያሉ ጉዳዮች ላይ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ ማምጣት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማምጣት ያስችላል በሚል እሳቤ ሲከናወኑ የቆዩ ስራዎች ውጤት ማስገኘታቸውን አመልክተዋል።

ባለፉት ዓመታት 27 ሚሊዮን ዜጎች በሴፍቲኔት ኢኒሼቲቭ በተረጂነት ማዕቀፍ ውስጥ እንደነበሩ አስታውሰዋል።

መንግስት ዜጎችን ከሴፍቴነት ነጻ ለማውጣት በግብርናው ንዑስ ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቷቸው ሲሰሩ ከነበሩ ጉዳዮች መካከል አንዱ እንደሆነ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በምስራቅ ሐረርጌ እና በደቡብ ሃላባ በነበራቸው ቆይታ አርሶ አደሮች ከሴፍቲኔት ተላቀው በራሳቸው አቅም ማምረት መጀመራቸውን እንደተመለከቱ አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ መለመን የለባትም ልጆቿ ተግተው ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው የሚለው እምነት ፍሬ እያፈረ መምጣቱን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት።

ዘንድሮ 23 ሚሊዮን ዜጎች ከሴፍቲኔት ተረጂነት ነጻ ወጥተዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ይህ የማንሰራራት እና ኢትዮጵያ ከጥገኝነት ለመላቀቅ የጀመረችው ስራ ትልቁ ማሳያ ነው ብለዋል።

በቀጣይ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ የጋራ ጥረት እና ርብርብ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025