የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በግብርና ዘርፍ ሜካናይዜሽን በመጠቀማችን ምርታማነት አድጓል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jul 4, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ በግብርናው ዘርፍ ሜካናይዜሽን የሚያስፋፉ በሺህ የሚቆጠሩ ትራክተሮችን በማስገባትና የመስኖ ልማትን በማስፋፋት ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታወቁ፡፡

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግብርናን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ሰፊ ሊታረስ የሚችል መሬት ካላቸው ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን አንስተዋል።

ለግብርናው ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት አምና 26 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ታርሶ አንድ ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ኩንታል ምርት ተገኝቶ እንደነበር አስታውሰዋል።

ዘንድሮ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት አጠቃላይ ሰላሳ ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ሄክታር መሬት ታርሶ አንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰቡን ገልጸዋል።

በዚህም ዘንድሮ ከአምናው አምስት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ሄክታር መሬት ጭማሪ በማረስ ሶስት መቶ ሚሊዮን ኩንታል ምርት ማግኘት ማቻሉን ነው ያብራሩት።

ግብርናውን ሜካናይዝድ ለማድረግና ምርትን ለማሳደግ በሺዎች የሚቆጠሩ ትራክተሮችና ፓምፖች ጥቅም ላይ መዋላቸውንና የግብርና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችም በእያንዳንዱ አርሶ አደር ማሳ ላይ ቀን ከሌት እየተጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በግብርናው ዘርፍ አዳዲስ የስራ ልምምድ መኖሩን ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሞቃታማ አካባቢዎች ማታ ጭምር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

ኖራን በማምረት ከ50ሺህ ሄክታር በላይ አሲዳማ መሬት ታክሞ ወደ እርሻ መግባቱን ገልፀው መሬትን ደጋግሞ የማረስና በአመት ሁለቴ ሶስቴ የማምረት ልምምድ ማደጉን በተለይ የበጋ መስኖ መጀመሩ ከፍተኛ እመርታ አምጥቷል ብለዋል፡፡

በሌማት ትሩፋት በዶሮ ልማት፣ የእንቁላልና የወተት ምርት ያደገበት፣ በሰው ሰራሽ ማዳቀል ዘዴ ምርታማነትን በመጨመር የወተት ፍጆታ በግለሰብ 66 ሊትር የነበረው ወደ 80 ሊትር ማደጉንም ተናግረዋል፡፡

በማር እና በአሳ የታዩ ከፍተኛ ለውጦች እንደ መልካም ጅማሮ የሚወሰዱና ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን መተካት መቻሉን በመጥቀስ ይህ ተጠናክሮ ሲቀጠል በብዙ ዘርፍ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል አውስተዋል፡፡

በቡና፣ በሻይና በሩዝ ልማት ላይም ለውጥ መኖሩን ጠቅሰው ግብርናው ትኩረት የተሰጠውና ትልቅ ውጤት ያመጣ እንዲሁም ለአጠቃላይ እድገታችን ትልቅ ድርሻ ያለው ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025