የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በድሬዳዋ ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል

Jul 4, 2025

IDOPRESS

ድሬደዋ፣ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ) ፡- በድሬዳዋ አስተዳደር ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ያህል ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የአስተዳደሩ ገቢዎች ባለስልጣን ገለጸ።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልሰላም መሐመድ በመሠረታዊ የታክስ ህጎች ላይ ለግብር ከፋዮች ለሁለት ሳምንታት የተሰጠው ስልጠና ዛሬ በተጠናቀቀበት ወቅት እንዳሉት፤ ገቢን ባለው አቅም ልክ ለመሰብሰብ ትኩረት ተሰጥቷል።

በዚህም ባለስልጣኑ በአስተዳደሩ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች የሚመነጨውን ሃብት የሚመጥን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በፍጥነትና በፍትሃዊነት እንዲመለሱ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በተለይ በለውጡ ዓመታት የሚሰበሰበው ዓመታዊ ገቢ በቢሊዮን ብር ደረጃ እየጨመረ ቢሆንም ኢኮኖሚው የሚያመነጨው ያህል ገቢ እየተሰበሰበ አለመሆኑን አንስተዋል።

ችግሩን ለመፍታት የሚያግዙ የተለያዩ የአሠራር ለውጦች ከማድረግ ባለፈ ታማኝ ግብር ከፋዮችን በስፋት ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።

ሰልጣኞቹም የዚሁ ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ይሄው ተግባር በአዲሱ የበጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል ።

የባለስልጣኑ የግብር ከፋዮች ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር አቶ አክሊለ ታጠቅ፤ ኢኮኖሚው የሚያመነጨው ያህል ገቢ በብቃት ለመሰብሰብ ለህግ ተገዢ የሆኑ ግብር ከፋዮችን ማፍራት አንዱ እርምጃ መሆኑን ተናግረዋል ።


ዛሬ ስልጠናቸውን ያጠናቀቁት ግብር ከፋዮች በሁሉም የታክስ ህጎች ላይ መሠረታዊ ዕውቀት በማግኘታቸው በቀጣይ መብታቸውን አስከብረው ያለባቸውን ግዴታ በትክክል ለመወጣት ያስችላቸዋል ብለዋል።

ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል አቶ አያሌው አለሙና አቶ ሙሉጌታ ብርሃኑ በሰጡት አስተያየት፤ በቆይታቸው ስለ ታክስ የተሻለ ዕውቀት መጨበጣቸውንና ለሁሉም ግብር ከፋይ መዳረስ ያለበት መሆኑን ተናግረዋል ።

በታማኝነት የሚከፍሉት ግብር ለራሳቸውና ለሀገር ዕድገትና ለውጥ የሚውል መሆኑን እንደሚረዱ ገልጸዋል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለታማኝ ግብር ከፋዮች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ላይ ይበልጥ ትኩረት ማድረግ እንዳለበትም ጠቁመዋል።

በስልጠናው 64 የተለያዩ ተቋማት ግብር ከፋዮች፣ ሥራ አስኪያጆችና ከፍተኛ የሂሳብ ባለሙያዎች መሳተፋቸው ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025