
ድሬደዋ፣ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ) ፡- በድሬዳዋ አስተዳደር ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ያህል ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የአስተዳደሩ ገቢዎች ባለስልጣን ገለጸ።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልሰላም መሐመድ በመሠረታዊ የታክስ ህጎች ላይ ለግብር ከፋዮች ለሁለት ሳምንታት የተሰጠው ስልጠና ዛሬ በተጠናቀቀበት ወቅት እንዳሉት፤ ገቢን ባለው አቅም ልክ ለመሰብሰብ ትኩረት ተሰጥቷል።
በዚህም ባለስልጣኑ በአስተዳደሩ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች የሚመነጨውን ሃብት የሚመጥን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በፍጥነትና በፍትሃዊነት እንዲመለሱ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በተለይ በለውጡ ዓመታት የሚሰበሰበው ዓመታዊ ገቢ በቢሊዮን ብር ደረጃ እየጨመረ ቢሆንም ኢኮኖሚው የሚያመነጨው ያህል ገቢ እየተሰበሰበ አለመሆኑን አንስተዋል።
ችግሩን ለመፍታት የሚያግዙ የተለያዩ የአሠራር ለውጦች ከማድረግ ባለፈ ታማኝ ግብር ከፋዮችን በስፋት ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።
ሰልጣኞቹም የዚሁ ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ይሄው ተግባር በአዲሱ የበጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል ።
የባለስልጣኑ የግብር ከፋዮች ትምህርትና ስልጠና ዳይሬክተር አቶ አክሊለ ታጠቅ፤ ኢኮኖሚው የሚያመነጨው ያህል ገቢ በብቃት ለመሰብሰብ ለህግ ተገዢ የሆኑ ግብር ከፋዮችን ማፍራት አንዱ እርምጃ መሆኑን ተናግረዋል ።

ዛሬ ስልጠናቸውን ያጠናቀቁት ግብር ከፋዮች በሁሉም የታክስ ህጎች ላይ መሠረታዊ ዕውቀት በማግኘታቸው በቀጣይ መብታቸውን አስከብረው ያለባቸውን ግዴታ በትክክል ለመወጣት ያስችላቸዋል ብለዋል።
ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል አቶ አያሌው አለሙና አቶ ሙሉጌታ ብርሃኑ በሰጡት አስተያየት፤ በቆይታቸው ስለ ታክስ የተሻለ ዕውቀት መጨበጣቸውንና ለሁሉም ግብር ከፋይ መዳረስ ያለበት መሆኑን ተናግረዋል ።
በታማኝነት የሚከፍሉት ግብር ለራሳቸውና ለሀገር ዕድገትና ለውጥ የሚውል መሆኑን እንደሚረዱ ገልጸዋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለታማኝ ግብር ከፋዮች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ላይ ይበልጥ ትኩረት ማድረግ እንዳለበትም ጠቁመዋል።
በስልጠናው 64 የተለያዩ ተቋማት ግብር ከፋዮች፣ ሥራ አስኪያጆችና ከፍተኛ የሂሳብ ባለሙያዎች መሳተፋቸው ተመልክቷል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026