
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2017(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለመንገድ ግንባታ የሰጠውን ትኩረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ 21 ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
በምረቃ መርሃ ግብሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ቡዜና አልከድር እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የሀይማኖት አባቶች አባገዳዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንደገለጹት፤ ከተማ አስተዳደሩ ከተማዋን ለማዘመን ከኮሪደር ልማት ስራዎች ባሻገር የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
በበጀት አመቱ ከተማ አስተዳደሩ የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ ፕሮጀክቶች ማከናወኑን ገልጸዋል።
በዛሬው እለት 31 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸዉ 13 የመንገድ ፕሮጀክቶችንና 8 ድልድዮችን አጠቃላይ 21 ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ተናግረዋል።

ፕሮጀክቶቹ በመንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ የተከናወኑ መሆናቸውን ያመላከቱት ከንቲባዋ፤ በዋናነት የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል።
በቀጣይ ለእድገት ዋና መሰረት የሆነውን የመንገድ መሰረተ ልማት ግንባታ ከተማ አስተዳደሩ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።
የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሞዲን ረሻድ(ኢ/ር) በበኩላቸው፤ ከተማ አስተዳደሩ ባለፉት ዓመታት ባከናወናቸው የመሰረተ ልማት ግንባታ በርካታ መንገዶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል ብለዋል።
በ2017 በጀት ዓመት የአስፓልት የኮብልስቶን ንጣፍ ጠጠር መንገድ የእግረኛ መንገድ የድጋፍ ግንብ እና የማፋሰሻ ቦዮች ግንባታዎችን ጨምሮ 371 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የመንገድ መሰረተ ልማት መገንባቱን ተናግረዋል።
በዚህ ምረቃ ግዙፍ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች የሆኑት የቃሊቲ ቱሉ ዲምቱ እና የቃሊቲ ቅሊንጦ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እንደሚገኙበትም ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025