የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ወጣቶች በሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jul 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2017(ኢዜአ)፦ ወጣቶች የትኛውንም አስቸጋሪ ሁኔታ ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር በሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስገነዘቡ።

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ተካሒዷል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጉባኤው ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ለአብነትም ከተማ አስተዳደሩ በአመራር ዘርፍ የወጣቶችን ተሳትፎ ለማረጋገጥ አካታች የፖለቲካ ስርዓትን ተግባራዊ ማድረጉን አንስተዋል።

እንዲሁም የወጣቶች ሰብዕና መገንቢያ ማዕከላት፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ጨምሮ የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሁኔታ ማመቻቸት የከተማ አስተዳደሩ የትኩረት አቅጣጫ ነው ብለዋል።

የብልፅግና ጉዞን ከዳር ለማድረስ የሚደረገውን ጥረት ለመምራት ወጣቶች በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባም ነው ከንቲባዋ ያስገነዘቡት።

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በስነ-ምግባር የታነፁ በእውቀትና በአቅም የዳበሩ ወጣቶችን ማፍራት ላይ እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ገልጸዋል።

ወጣቶች የትኛውንም አስቸጋሪ ሁኔታ ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር በሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።


የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ በላይ ደጀን በበኩላቸው የከተማዋ ወጣቶች በሰላም ግንባታ፣ በአረንጓዴ አሻራና መሰል የልማት ስራዎች ላይ የሚያደርጉት ተሳትፎ ላቅ ያለ መሆኑን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በበጎ ፍቃድ አገልግሎት በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን እየተወጡ ስለመሆኑም አንስተዋል።

ከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ባከናወናቸው ተግባራት አዲስ አበባን የሰላም፣ የፍቅርና የአብሮነት ከተማ እንድትሆን ማድረግ ችሏል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ሰብሳቢ ገዛኸኝ ገብረማሪያም፤ ማህበሩ ወጣቶች በሀገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እየተወጣ መሆኑን ገልጿል።

በመንግሥት የሚከናወኑ የልማትና መሰል ተግባራትን በማጠናከር ሒደት ወጣቱ በባለቤትነት እንዲሳተፍ የተለያዩ መርሃ-ግብሮችን በማዘጋጀት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑንም አብራርቷል።

በተለይም ወጣቱ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ በስራ ዕድል እና በኮሪደር ልማት ስራ እና በሌሎች ዘርፎች ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን ማህበሩ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ጠቁሟል።

በዚህም መንግስት የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የፈጠረውን ምህዳር ለመጠቀም አስቻይ ሁኔታ ፈጥሯል ብሏል።


በጉባኤው ላይ ማህበሩን በተለያየ መልኩ ለሚያግዙ ተቋማትና ማህበራት እውቅና የመስጠት መርሃ-ግብርም ተካሒዷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026