የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ በአስደናቂ የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች- የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀመድ አሊ የሱፍ

Jul 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30 /2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በብዝሃ የኢኮኖሚ ዘርፍ በአስደናቂ የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀመድ አሊ የሱፍ ገለጹ።

ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳል አመራር በአስደናቂ የለውጥ ጎዳና ላይ እንደምትገኝም ተናግረዋል።

3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም መካሄድ ጀምሯል።

በፎረሙ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች፣ የፈጠራ ባለሙያዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች፣ የዘርፉ ምሁራን እና ባለድርሻ አካላት ታድመዋል።


የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀመድ አሊ የሱፍ፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እንድታስመዘግብ እየሰጡ ላለው ድንቅ አመራርም አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

በአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራን እና የኢኮኖሚ ለውጥን ማሳካት የልማት ዋነኛ መሠረት ነው ብለዋል።

ወጣቶችና ሴቶች የዲጂታል ክህሎት ስልጠና እና የፋይናንስ ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግም ይገባል ነው ያሉት።

በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ አስደናቂ ስኬት እያስመዘገበች መሆኗን ገልጸዋል።

አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ የኢትዮጵያ ከተሞች በአስደናቂ እና ህይወት ቀያሪ የዕድገት ጉዞ ላይ መሆናቸውን ገልጸው፥ ይህም የድንቅ አመራር ውጤት ማሳያ ነው ብለዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አመራር ኢትዮጵያ በግብርናው መስክም በስንዴና ሌሎች የሰብል ምርቶች ራስን ከመቻል አልፋ ኤክስፖርት እስከማድረግ ደርሳለች ነው ያሉት።

ከአፍሪካ ህዝብ ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው ከ25 ዓመት በታች ዕድሜ ላይ የሚገኝ ወጣት ኃይል መሆኑን በማውሳት፥ በየዓመቱ የሚፈጠረው የሥራ ዕድል አሁንም አነስተኛ ነው ብለዋል።

አፍሪካ በዓለም የምርት እሴት ሰንሰለት ውስጥ ያላት ድርሻም ከሦስት በመቶ በታች መሆኑን በማንሳት ይህን ከፍ ማድረግ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።

ግብርና በአፍሪካ ከፍተኛ የሥራ ዕድል መፍጠሪያ መስክ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከ60 በመቶ በላይ ህዝብ ህይወቱን የሚመራበትም ነው ብለዋል።

የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣናም ለሥራ ዕድል ፈጠራ ተጨማሪ አቅም እንደሆነ በማንሳት፥ ወደ ተግባር ማስገባት አለብን ብለዋል።

የግሉ ዘርፍ፣ አነስተኛና ከፍተኛ ድርጅቶች በነፃ የንግድ ቀጣናው በመሳተፍ ተጠቃሚ ለመሆን እንዲዘጋጁም ጥሪ አቅርበዋል።


ቴክኖሎጂን በማስፋፋት አዳዲስ ሥራዎችን የመፍጠርን አስፈላጊነት በማንሳት፥ የወጣቶች ፈጠራን በማበረታታት ፈተናዎችን የሚቋቋም ዲጂታል ሥርዓትን እንዲገነቡ ማድረግ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

በሁሉም መስክ አካታች ልማትን እውን በማድረግ ድህነትን ከአፍሪካ የማጥፋት ግብን ለማሳካት የጋራ ሥራ ወሳኝ መሆንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025