የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአፍሪካ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የሚደረጉ ትብብሮች እንዲሳለጡ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት ትሰራለች - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Jul 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የሚደረጉ ትብብሮች እንዲሳለጡ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት ትሰራለች ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

በፎረሙ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀመድ አሊ የሱፍ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች፣ የፈጠራ ባለሙያዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎችና የዘርፉ ምሁራን እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ፎረሙ አፍሪካ ያላትን እምቅ ሀብት ወደ ተጨባጭ አቅም ለመቀየር፣ ሥራ አጥነትን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ፣ ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትንና አህጉራዊ ትስስርን ማላቅ ዓላማ አድርጎ ላለፉት ሁለት ተከታታይ ዓመታት ሲካሄድ ቆይቷል፡፡


ዘንድሮም ለሦስተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ከዛሬ ጀምሮ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በመካሄድ ላይ ሲሆን እስከ ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ለሥራ ዕድል ፈጠራ በተሰጠው ትኩረት በአማካኝ በየዓመቱ ለ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።

ለሥራ ፈጠራው ምቹ ሥነ ምህዳር የመፍጠሩ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም አንስተዋል።

ከግሉ ዘርፍ፣ ከሴክተር መስሪያ ቤቶችና ከቀጣናዊ የልማት አጋሮች ጋር የተፈጠረው የትብብር አውድ መልካም ውጤቶች እንዲገኙ ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ ነው ብለዋል።

ዛሬ መገናኘታችን በርካታ ፋይዳዎች አሉት ያሉት ሚኒስትሯ የጋራ እጣ ፈንታችንን በጋራ እና በህብረት ለመጻፍ መነሳት እንዳለብን የሚያመላክት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ወቅቱ የሚጠይቀው አርበኝነት ጠንካራ የሥራ ባህል መገንባት በመሆኑ በትብብር መሥራት ይገባል ነው ያሉት።


በሥራ ዕድል ፈጠራ በኩል በአፍሪካ የሚደረጉ ትብብሮች እንዲሳለጡ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እንደምትሰራም ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።

በአፍሪካ በየዓመቱ 30 ሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ገበያውን የሚቀላቀሉ መሆኑን ጠቅሰው፤ እንዲያም ሆኖ በርካታ ተመራቂ ወጣቶች አሁንም ሥራ ይፈልጋሉ ብለዋል።

ሚኒስትር ሙፈሪሃት ክህሎትና ሥራ ዕድል ፈጠራዎች አሁንም ያልተሻገርናቸው የቤት ሥራዎች ናቸው ሲሉም አንስተዋል።

ፎረሙ በይፋ ሲጀመር እንደ አህጉር በሚቀጥሉት 15 ዓመታት ከ80 እስከ 125 ሚሊዮን ለሚደርሱ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ግብ መያዙን አስታውሰው፤ ግቡ ብዙ ሥራ የሚጠይቅ ሆኖ በትብብርና በቁርጠኝነት ከተሰራ ሊሳካ የሚችል ነው ሲሉም አብራርተዋል።

በመድረኩ የግብርና እሴት ሰንሰለት፣ ዲጂታላይዜሽንና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ በተለይ ለሴቶችና ወጣቶች ምቹና አስተማማኝ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትስስርን ማላቅ ላይ ያተኮረ ምክክር ይደረጋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026