የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ እያከናወነች ያለው ተግባር አስደናቂ ነው -የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ተሳታፊ ሚኒስትሮች

Jul 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እድገቷን ለማፋጥን በቴክኖሎጂ ዘርፍ እያከናወነች ያለው ተግባር አስደናቂና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን በ3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ተሳታፊ የሆኑ ሚኒስትሮችና የስራ ሃላፊዎች ገለጹ፡፡

የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ሚኒስትሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ የዘርፉ ምሁራን፣ ተመራማሪዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ተሳታፊዎቹ ትናንት ከሰዓት በኋላ የአድዋ ድል መታሰቢያን፣ ሳይንስ ሙዚየምንና የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማትን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት አስተያየታቸውን ከሰጡን መካከል የጋና የሠራተኛ፣ ሥራና የሥራ ስምሪት ሚኒስትር አብዱል-ራሺድ ፔልፑዎ ፤ አዲስ አበባ በፈጣን እድገት ላይ መሆኗን መመልከታቸውን ተናግረዋል።


የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹ የከተማዋን እድገት የሚያፋጥኑ መሆናቸውን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ እድገቷን ለማፋጠን የጀመረቻቸው ተግባራት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ምሳሌ ናቸው ብለዋል።

የደቡብ ሱዳን የሰራተኞች ጉዳይ ሚኒስትር ጀነራል ጄምስ ሆት ማይ በበኩላቸው በሳይንስ ሙዚየም ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ እያከናወነች ያለውን ስራ መመልከታቸውን ነው የተናገሩት።

የተመለከቷቸው ስራዎች ኢትዮጵያ ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ዘመናዊ እርሻ ላይ ያላትን ዕቅድ የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።


ኢትዮጵያ የጀመረቻቸው ተግባራት በአፍሪካ ከምግብ ዋስትና ጋር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚሆን የልማት ስራ እያከናወነች እንደምትገኝ የገለጹት ደግሞ በማላዊ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ልማት ላይ የሚሰራ ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ቦንፊስካ ዛሚራ ናቸው።


በሳይንስ ሙዚየም በተመለከቱት ስራ መደነቃቸውን የገለጹት ቦንፊስካ፤ ተግባራቱ ኢትዮጵያን በዘርፉ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሀገር ያደርጋታል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026