
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እድገቷን ለማፋጥን በቴክኖሎጂ ዘርፍ እያከናወነች ያለው ተግባር አስደናቂና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን በ3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም ተሳታፊ የሆኑ ሚኒስትሮችና የስራ ሃላፊዎች ገለጹ፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 3ኛው የአፍሪካ የስራ ፈጠራ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ሚኒስትሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ የዘርፉ ምሁራን፣ ተመራማሪዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ተሳታፊዎቹ ትናንት ከሰዓት በኋላ የአድዋ ድል መታሰቢያን፣ ሳይንስ ሙዚየምንና የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማትን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት አስተያየታቸውን ከሰጡን መካከል የጋና የሠራተኛ፣ ሥራና የሥራ ስምሪት ሚኒስትር አብዱል-ራሺድ ፔልፑዎ ፤ አዲስ አበባ በፈጣን እድገት ላይ መሆኗን መመልከታቸውን ተናግረዋል።

የመሰረተ ልማት ግንባታዎቹ የከተማዋን እድገት የሚያፋጥኑ መሆናቸውን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ እድገቷን ለማፋጠን የጀመረቻቸው ተግባራት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ምሳሌ ናቸው ብለዋል።
የደቡብ ሱዳን የሰራተኞች ጉዳይ ሚኒስትር ጀነራል ጄምስ ሆት ማይ በበኩላቸው በሳይንስ ሙዚየም ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ዘርፍ እያከናወነች ያለውን ስራ መመልከታቸውን ነው የተናገሩት።
የተመለከቷቸው ስራዎች ኢትዮጵያ ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ዘመናዊ እርሻ ላይ ያላትን ዕቅድ የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

ኢትዮጵያ የጀመረቻቸው ተግባራት በአፍሪካ ከምግብ ዋስትና ጋር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ የሚሆን የልማት ስራ እያከናወነች እንደምትገኝ የገለጹት ደግሞ በማላዊ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ልማት ላይ የሚሰራ ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ቦንፊስካ ዛሚራ ናቸው።

በሳይንስ ሙዚየም በተመለከቱት ስራ መደነቃቸውን የገለጹት ቦንፊስካ፤ ተግባራቱ ኢትዮጵያን በዘርፉ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሀገር ያደርጋታል ብለዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026