
ሮቤ ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦በሮቤ ከተማ የግብር አሰባሰብ ስርዓትን ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚጠናከሩ የከተማው ገቢዎች ጽህፈት ቤት ገለጸ።
የሮቤ ከተማና የዞኑ ገቢዎች ጽህፈት ቤት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች የንቅናቄ መድረክ አካሄደዋል።
የሮቤ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ መሰለች በዬቻ እንዳሉት በከተማው የግብር አሰባሰብ ስርዓትን በማዘመን ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል።
በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከተለያዩ አርዕስቶች ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።

በዘንድሮ የበጀት ዓመትም የገቢ አሰባሰብ ሂደትን በማዘመንና አዳዲስ የገቢ አማራጮችን በመፈተሽ ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ የደረጃ ´´ሐ´´ የግብር ከፋዮችን ያሳተፈ የንቅናቄ መድረክ መጀመሩን ተናግረዋል።
በዚህም በከተማዋ ከ8 ሺህ የሚበልጡ የደረጃ ´´ሐ´´ የግብር ከፋዮችን በማሳተፍ ትናንት በተካሄደ የግብር ንቅናቄ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።
በሌላ በኩል በባሌ ዞን በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የዞኑ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታጁዲን ሀሱ ተናግረዋል።

በአዲሱ የበጀት ዓመት የግብር አሰባሰብ ሂደትን ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ ከ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል።
በተለይ የግብር ስወራን በመቆጣጠር፣ ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ግብር መረቡ ማስገባት በአዲሱ በጀት ዓመት ትኩረት ከሚሰጣቸው ስራዎች መካከል ዋናኞቹ መሆናቸውን አቶ ታጁዲን ጠቅሰዋል።
በሮቤ ከተማ የደረጃ 'ሐ' የግብር ከፋዮች መካከል አቶ መሐመድ ከድር በሰጡት አስተያየት ግብርን በአግባቡ መክፈል ለአገር ልማት ያለው አስተዋጽኦ ትልቅ በመሆኑ የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ እንደሚከፍሉ ተናግረዋል።

አቶ አህመድ ማህሙድ በበኩላቸው የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ በመምጣቱ ግብርን በወቅቱ ለመክፈል እንዳነሳሳቸው ገልጸዋል።

በሮቤ ከተማ አስተዳደር እና የባሌ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች 20 ሺህ የሚሆኑ የግብር ከፋዮች የሚገኙ ሲሆን ከነዚህ መካከል 88 ነጥብ 7 በመቶ የሚሆኑት የደረጃ ´´ሐ´´ የግብር ከፋዮች መሆናቸው ተጠቁሟል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025