የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በከተማው የግብር አሰባሰብ ስርዓትን ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ስራዎች ይጠናከራሉ

Jul 10, 2025

IDOPRESS

ሮቤ ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦በሮቤ ከተማ የግብር አሰባሰብ ስርዓትን ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚጠናከሩ የከተማው ገቢዎች ጽህፈት ቤት ገለጸ።

የሮቤ ከተማና የዞኑ ገቢዎች ጽህፈት ቤት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች የንቅናቄ መድረክ አካሄደዋል።

የሮቤ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ መሰለች በዬቻ እንዳሉት በከተማው የግብር አሰባሰብ ስርዓትን በማዘመን ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል።

በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከተለያዩ አርዕስቶች ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።


በዘንድሮ የበጀት ዓመትም የገቢ አሰባሰብ ሂደትን በማዘመንና አዳዲስ የገቢ አማራጮችን በመፈተሽ ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ የደረጃ ´´ሐ´´ የግብር ከፋዮችን ያሳተፈ የንቅናቄ መድረክ መጀመሩን ተናግረዋል።

በዚህም በከተማዋ ከ8 ሺህ የሚበልጡ የደረጃ ´´ሐ´´ የግብር ከፋዮችን በማሳተፍ ትናንት በተካሄደ የግብር ንቅናቄ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።

በሌላ በኩል በባሌ ዞን በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የዞኑ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታጁዲን ሀሱ ተናግረዋል።


በአዲሱ የበጀት ዓመት የግብር አሰባሰብ ሂደትን ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ ከ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል።

በተለይ የግብር ስወራን በመቆጣጠር፣ ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ግብር መረቡ ማስገባት በአዲሱ በጀት ዓመት ትኩረት ከሚሰጣቸው ስራዎች መካከል ዋናኞቹ መሆናቸውን አቶ ታጁዲን ጠቅሰዋል።

በሮቤ ከተማ የደረጃ 'ሐ' የግብር ከፋዮች መካከል አቶ መሐመድ ከድር በሰጡት አስተያየት ግብርን በአግባቡ መክፈል ለአገር ልማት ያለው አስተዋጽኦ ትልቅ በመሆኑ የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ እንደሚከፍሉ ተናግረዋል።


አቶ አህመድ ማህሙድ በበኩላቸው የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ በመምጣቱ ግብርን በወቅቱ ለመክፈል እንዳነሳሳቸው ገልጸዋል።


በሮቤ ከተማ አስተዳደር እና የባሌ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች 20 ሺህ የሚሆኑ የግብር ከፋዮች የሚገኙ ሲሆን ከነዚህ መካከል 88 ነጥብ 7 በመቶ የሚሆኑት የደረጃ ´´ሐ´´ የግብር ከፋዮች መሆናቸው ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026