
ሮቤ ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦በሮቤ ከተማ የግብር አሰባሰብ ስርዓትን ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚጠናከሩ የከተማው ገቢዎች ጽህፈት ቤት ገለጸ።
የሮቤ ከተማና የዞኑ ገቢዎች ጽህፈት ቤት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች የንቅናቄ መድረክ አካሄደዋል።
የሮቤ ከተማ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ መሰለች በዬቻ እንዳሉት በከተማው የግብር አሰባሰብ ስርዓትን በማዘመን ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል።
በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከተለያዩ አርዕስቶች ከ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።

በዘንድሮ የበጀት ዓመትም የገቢ አሰባሰብ ሂደትን በማዘመንና አዳዲስ የገቢ አማራጮችን በመፈተሽ ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ የደረጃ ´´ሐ´´ የግብር ከፋዮችን ያሳተፈ የንቅናቄ መድረክ መጀመሩን ተናግረዋል።
በዚህም በከተማዋ ከ8 ሺህ የሚበልጡ የደረጃ ´´ሐ´´ የግብር ከፋዮችን በማሳተፍ ትናንት በተካሄደ የግብር ንቅናቄ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።
በሌላ በኩል በባሌ ዞን በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከ2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የዞኑ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታጁዲን ሀሱ ተናግረዋል።

በአዲሱ የበጀት ዓመት የግብር አሰባሰብ ሂደትን ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ ከ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል።
በተለይ የግብር ስወራን በመቆጣጠር፣ ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ወደ ግብር መረቡ ማስገባት በአዲሱ በጀት ዓመት ትኩረት ከሚሰጣቸው ስራዎች መካከል ዋናኞቹ መሆናቸውን አቶ ታጁዲን ጠቅሰዋል።
በሮቤ ከተማ የደረጃ 'ሐ' የግብር ከፋዮች መካከል አቶ መሐመድ ከድር በሰጡት አስተያየት ግብርን በአግባቡ መክፈል ለአገር ልማት ያለው አስተዋጽኦ ትልቅ በመሆኑ የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱ እንደሚከፍሉ ተናግረዋል።

አቶ አህመድ ማህሙድ በበኩላቸው የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ በመምጣቱ ግብርን በወቅቱ ለመክፈል እንዳነሳሳቸው ገልጸዋል።

በሮቤ ከተማ አስተዳደር እና የባሌ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች 20 ሺህ የሚሆኑ የግብር ከፋዮች የሚገኙ ሲሆን ከነዚህ መካከል 88 ነጥብ 7 በመቶ የሚሆኑት የደረጃ ´´ሐ´´ የግብር ከፋዮች መሆናቸው ተጠቁሟል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026