
ሐመር-ዲመካ፤ ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)-በደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሩ በራስ አቅም የምግብ ዋስትናውን የሚያረጋግጥበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
በዞኑ የ2017/18 ምርት ዘመን የመኸር እርሻ ንቅናቄና የአመራር አባላት የአቅም ግንባታ መድረክ በዞኑ በዲመካ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ እንደገለጹት መንግስት በአርብቶ አደሩ አከባቢ የተረጅነት አመለካከትን በመቀየር ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎችን እያከናወነ ነው።
አርብቶ አደሩ ቀደም ሲል መተዳደሪያው በከብት እርባታ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አንስተው፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት በሰጠው ትኩረት ከከብት እርባታው ጎን ለጎን በመስኖ ልማት ተሳትፎ እንዲያደርግ እገዛ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል ።

ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች የመስኖ አውታሮችን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል ።
"በዚህም በዞኑ ባለፉት አመታት በተከናወኑ የግብርና ልማት ስራዎች አርብቶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን ከማረጋገጥ ባለፈ የኢኮኖሚ አቅሙን የሚያጎለብትበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል" ብለዋል።
አርብቶ አደሩ በመስኖ ልማት እያደረገ ያለው ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ምንላርገው አዲሱ ናቸው።

በዞኑ በተከናወኑ የግብርና ልማት ስራዎች የተረጅነት አመለካከት እየተቀረፈ መምጣቱን ተናግረዋል ።
በአሁኑ ሰአት በዞኑ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተው ጥጥ፣ ሙዝ፣ ማሾና ሰሊጥ የመሳሰሉ የግብርና ምርቶችንም ለማዕከላዊ ገበያ ከማቅረብ ባለፈ ወደ ጎረቤት ሀገራት ለገበያ እየተላኩ መሆኑን አስታውቀዋል ።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026