
ሐመር-ዲመካ፤ ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)-በደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሩ በራስ አቅም የምግብ ዋስትናውን የሚያረጋግጥበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
በዞኑ የ2017/18 ምርት ዘመን የመኸር እርሻ ንቅናቄና የአመራር አባላት የአቅም ግንባታ መድረክ በዞኑ በዲመካ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ እንደገለጹት መንግስት በአርብቶ አደሩ አከባቢ የተረጅነት አመለካከትን በመቀየር ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎችን እያከናወነ ነው።
አርብቶ አደሩ ቀደም ሲል መተዳደሪያው በከብት እርባታ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አንስተው፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት በሰጠው ትኩረት ከከብት እርባታው ጎን ለጎን በመስኖ ልማት ተሳትፎ እንዲያደርግ እገዛ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል ።

ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች የመስኖ አውታሮችን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል ።
"በዚህም በዞኑ ባለፉት አመታት በተከናወኑ የግብርና ልማት ስራዎች አርብቶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን ከማረጋገጥ ባለፈ የኢኮኖሚ አቅሙን የሚያጎለብትበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል" ብለዋል።
አርብቶ አደሩ በመስኖ ልማት እያደረገ ያለው ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ምንላርገው አዲሱ ናቸው።

በዞኑ በተከናወኑ የግብርና ልማት ስራዎች የተረጅነት አመለካከት እየተቀረፈ መምጣቱን ተናግረዋል ።
በአሁኑ ሰአት በዞኑ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተው ጥጥ፣ ሙዝ፣ ማሾና ሰሊጥ የመሳሰሉ የግብርና ምርቶችንም ለማዕከላዊ ገበያ ከማቅረብ ባለፈ ወደ ጎረቤት ሀገራት ለገበያ እየተላኩ መሆኑን አስታውቀዋል ።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025