የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በፈጠረው ሀይቅ ዓሳን በማምረት ተጠቃሚ ሆነናል - የግድቡ አካባቢ ነዋሪዎች

Jul 14, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ሐምሌ 5/2017 (ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከፈጠረው ሀይቅ ዓሳ በማምረት ተጠቃሚ መሆናቸውን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግድቡ አካባቢ ነዋሪዎች ገለጹ።

በኢትዮጵያውያን የጋራ ትብብር የተገነባው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ2018 ዓ.ም እንደሚመረቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት መግለጻቸው ይታወሳል።

ግድቡ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ከሚሰጠው ጥቅም ባሻገር ከግድቡ ሀይቅ የአካባቢው ነዋሪዎች ዓሳ እያመረቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የታላቁ የህዳሴ ግድብ ከፈጠረው ሀይቅ ዓሳን ከሚያመርቱ የሸርቆሌ እና ሰዳል ወረዳ ነዋሪዎች ጋር ኢዜአ ቆይታ ያደረገ ሲሆን፤ ነዋሪዎቹም ግድቡ በፈጠረው ሀይቅ ዓሳ እያመረቱ መሆኑን ገልጸዋል።

በዓሳ ምርቱ ከተሰማሩ የሸርቆሌ ወረዳ ነዋሪዎች መካከል አቶ አጅብ ሙሀመድ በህዳሴው ግድብ አማካኝነት ከተፈጠረው ሀይቅ ከሚያሰግሩት ዓሳ ቤተሰባቸውን እያስተዳደሩ ይገኛሉ።


የዓሳ ምርቱን ለገበያ እያቀረቡ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ከመሆናቸው ባለፈ ለምግብነት እየተጠቀሙ መሆኑንም ተናግረዋል።

የዚሁ ወረዳ ነዋሪ አቶ ዘካሪያ አጀሊ በበኩላቸው፤ በማህበር ተደራጅተው ዓሳን በማምረት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ምርታቸውንም ለአሶሳና ለሌሎች አካባቢዎች በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው ማደጉን ገልጸው በቀጣይ የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን እንደሚሰሩ ገልጸዋል።


ሌላው ዓሳን አዘጋጅቶ ለገበያ እያቀረበ የሚገኘው ኤሊያስ እና ጓደኞቹ ዓሳ አምራች ማህበር አባል ወጣት ደባሽ ትዜ፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከፈጠረው ሀይቅ ላይ የዓሳ ምርት በስፋት እያገኙ መሆኑን ተናግሯል።

በዓሳ ምርቱ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆኑን ጠቁሞ ማህበሩ 40 ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠሩን ገልጿል።


የሚያመርቱትን ዓሳ እስከ አዲስ አበባ ድረስ በራሳቸው ተሽከርካሪ በማጓጓዝ እየሸጡ መሆኑንም ጠቅሷል።

በቀን እስከ 20ሺህ ብር ገቢ እያገኙ መሆናቸውንና የኢኮኖሚ አቅማቸውን እያሳደጉ እንደሆነ የተናገሩት ደግሞ በሰዳል ወረዳ በዓሳ ምርት ላይ የተሰማሩት አቶ ነጅብ መኪና ናቸው።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ የእንስሳት እና ዓሳ ግብዓት አቅርቦት ባለሙያ አቶ ገመቹ አየለ፣ በ2017 በጀት ዓመት ከታላቁ ህዳሴ ግድብ 5ሺህ 895 ቶን የዓሳ ምርት መገኘቱን ተናግረዋል።


በህዳሴ ግድብ አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችም በዓሳ ምርት ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

ቢሮው ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር በማህበር ለተደራጁ ወጣቶች ጀልባ እና የዓሳ ማጥመጃ መረብ ድጋፍ ማድረጉንም ጠቅሰዋል።

የሚመረተው ዓሳ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲቀርብ ለማድረግ ትልልቅ ድርጅቶች ጥያቄ እያቀረቡ መሆናቸውንም ባለሙያው አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026