የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የገጠር ኮሪደር ልማት የኅብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ኢኒሼቲቭ ነው

Jul 14, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የገጠር ኮሪደር ልማት የኅብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ኢኒሼቲቭ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና ሴክተር ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ ገለጹ።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትና ተጠሪ ተቋማት በቤንች ሸኮ ዞን የገጠር ኮሪደር ልማትን እሳቤ አሟልተው የሚገነቡ አምስት ሞዴል ቤቶች ግንባታ ሥራን አስጀምረዋል።


በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና ሴክተር ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ እንዳሉት የገጠር ኮሪደር ልማት እሳቤ የገጠር ነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ሀገራዊ ኢኒሼቲቭ ነው።

በዚህም ለአርሶ እና አርብቶ አደሩ ጤናማና ምቹ የአኗኗር ስርአት ከመፍጠር ባለፈ ከምርታማነት ጋር ለማስተሳሰር ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም የሞዴል ቤቶች ግንባታ ጽዳቱን የጠበቀ መኖሪያ ቤት ከመገንባት ጀምሮ የሌማት ትሩፋት፣ የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የአረንጓዴ ሥፍራና ለማኅበራዊ አገልግሎት የሚውሉ መስኮችን ያካተተ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ለዚህም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የገጠር ኮሪደር እሳቤን ታሳቢ ያደረጉ አምስት ሞዴል ቤቶችን በጉራፈርዳ ወረዳ እንደሚገነባና ከእዚህም ሌሎች አይተው እንዲያስፋፉ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል።

የገጠር ኮሪደር ልማት ተግባር የገጠር ነዋሪዎች አኗኗርን ዘመናዊ በማድረግ ለብልጽግና ጉዞ ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑንም ነው ሚኒስትር ዴኤታው የተናገሩት።


የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የከተማና የገጠር ነዋሪዎችን ያማከለ የልማት ኢኒሼቲቮችን በመዘርጋት ሁሉንም ተጠቃሚ ለማድረግ እየሠራ ነው ብለዋል።

በክልሉ የተለያዩ ቀበሌዎች የተጀመሩ የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸው፣ ልማቱንም በምግብ ራስን ለመቻል ከሚሰራው ሥራ ጋር ማቆራኘት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025