
ሚዛን አማን፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የገጠር ኮሪደር ልማት የኅብረተሰቡን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ኢኒሼቲቭ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና ሴክተር ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ ገለጹ።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትና ተጠሪ ተቋማት በቤንች ሸኮ ዞን የገጠር ኮሪደር ልማትን እሳቤ አሟልተው የሚገነቡ አምስት ሞዴል ቤቶች ግንባታ ሥራን አስጀምረዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የካቢኔ ጉዳዮችና ሴክተር ክትትል ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ እንዳሉት የገጠር ኮሪደር ልማት እሳቤ የገጠር ነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ትልቅ ሀገራዊ ኢኒሼቲቭ ነው።
በዚህም ለአርሶ እና አርብቶ አደሩ ጤናማና ምቹ የአኗኗር ስርአት ከመፍጠር ባለፈ ከምርታማነት ጋር ለማስተሳሰር ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም የሞዴል ቤቶች ግንባታ ጽዳቱን የጠበቀ መኖሪያ ቤት ከመገንባት ጀምሮ የሌማት ትሩፋት፣ የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የአረንጓዴ ሥፍራና ለማኅበራዊ አገልግሎት የሚውሉ መስኮችን ያካተተ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የገጠር ኮሪደር እሳቤን ታሳቢ ያደረጉ አምስት ሞዴል ቤቶችን በጉራፈርዳ ወረዳ እንደሚገነባና ከእዚህም ሌሎች አይተው እንዲያስፋፉ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ተግባር የገጠር ነዋሪዎች አኗኗርን ዘመናዊ በማድረግ ለብልጽግና ጉዞ ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑንም ነው ሚኒስትር ዴኤታው የተናገሩት።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የከተማና የገጠር ነዋሪዎችን ያማከለ የልማት ኢኒሼቲቮችን በመዘርጋት ሁሉንም ተጠቃሚ ለማድረግ እየሠራ ነው ብለዋል።
በክልሉ የተለያዩ ቀበሌዎች የተጀመሩ የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸው፣ ልማቱንም በምግብ ራስን ለመቻል ከሚሰራው ሥራ ጋር ማቆራኘት እንደሚገባ ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025