የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በዞኑ የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች ምርትና አገልግሎታቸውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው

Jul 15, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፤ ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፡- በምስራቅ ቦረና ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የስራ እድል የተፈጠረላቸው ወጣቶች ምርትና አገልግሎታቸውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ ተገለጸ።

በዞኑ የስራ እድል ፈጠና ክህሎት ጽህፈት ቤት የስራ እድል ፈጠራ ቡድን መሪ አቶ ጎዳና ሳራ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በዞኑ ለ42ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መመቻቸቱን ለኢዜአ ተናግረዋል።


ከእነዚህም መካከል ከ10ሺህ 560 በላይ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ሰልጥነው የተመረቁ ናቸው ብለዋል፡፡

ነገሌ ቦረና ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ አጠቃላይ በዞኑ ወደ ስራ ከገቡት ወጣቶች መካከል 15ሺህ 971 ሴቶች እንደሆኑም አንስተዋል፡፡

ወጣቶቹ ወደ ስራ የገቡት በግብርና፣ በአገልግሎትና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ሲሆን፤ ግንባታ፣ ንግድ፣ እንስሳት እርባታ፣ ማዕድን ፍለጋና ግብይት፤ የቤትና የቢሮ እቃዎች ማመርተ ሰፊውን ድርሻ ይወስዳሉ ብለዋል።

ወደ ስራ ለገቡት ወጣቶች 78 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ብድር በማመቻቸት ትራክተር፣ ከ10 ሄክታር በላይ የማምረቻ እና መሸጫ ቦታና 61 የመሸጫ ሱቆች ድጋፍ መደረጉን አስታውቀዋል፡፡


ወደ ስራ የገቡ ወጣቶችምምርትና አገልግሎታቸውን በብዛትና በጥራት ለገበያ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

የነገሌ ቦረና ከተማ ነዋሪ አልዬ ዋቆ ከ3 ባልደረቦቹ ጋር በልብስ ስፌትና የአልባሳት ምርት አቅርቦት ስራ ከተሰማሩ ወጣቶች መካከል አንዱ ሲሆን፤አልባሳቱ ባህልን ከማስተዋወቅ ባለፈ በገበያ አዋጭ በመሆኑ የተሻለ ገቢ የሚያስገኝ ተመራጭ የስራ ዘርፍ መሆኑን ገልጿል፡፡

በውጤቱም እራሳችንንና ቤተሰቦቻችንን ከመርዳት አልፈን ከንግድ ስራው የምናገኘውን ትርፍ መቆጠብ ጀምረናል ሲልም ተናግሯል፡፡

ሌላው የከተማው ነዋሪ ወጣት ቢኒያም አምሳሉና 2 ባልደረቦቹ በብረታ ብረት የስራ ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።

ወጣት ቢኒያም በሰጠው አስተያየት፤ ምርታችንን በጥራት እያመረትን ለነገሌ ቦረና ከተማ ህዝብና ለሴክተር መስሪያ ቤቶች ጭምር እያቀረብን ነው ብሏል።

አሁን ላይ ካፒታላቸው 150ሺህ ብር መድረሱን ገልጸው በቀጣይም ስራቸውን ለማስፋፋት ተጨማሪ ብድር ለመውሰድ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025