
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017(ኢዜአ)፦ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የዲጂታል እውቀትን በማስፋፋት፣ የግለሰቦችንና የተቋማትን የመፈጸም አቅም ማጎልበትን ቁልፍ ዓላማ ያደረገ መሆኑን የኢኖቬሸን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር "በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ረቂቅ ስትራቴጂ ሰነድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል።

ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የተገኙ ስኬቶች ላይ ተመስርቶ አዳዲስ የዲጂታል እድገቶች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
ስትራቴጂው ከአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና የዲጂታል የህዝብ መሰረተ ልማት እስከ ስማርት ከተሞች፣ ድንበር ተሻጋሪ ኢ-ኮሜርስ፣ ዲጂታል ሉዓላዊነት የመሳሰሉ ጽንሰ ሃስቦችን አካቶ የተዘጋጀ ነው ብለዋል።
ስትራቴጂው ቴክኖሎጂን በመጠቀም ስለሚፈጠሩ የስራ እድሎች፣ አካታችና ፍትሃዊ ልማትን እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልጽግናን አላማ አድርጎ የተነደፈ መሆኑንም ተናግረዋል።

የዲጂታል እውቀትን በማስፋፋትና የተቋም አቅምን በመገንባት የግለሰቦችን እንዲሁም የተቋማትን የመፈጸም አቅም ማጎልበት ከስትራቴጂው ዋና አላማዎች መካከል እንደሆነም ገልጸዋል።
አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ እድገትን ማፋጠን፣ ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ተደራሽነትን ማሳደግ እና ኢትዮጵያን ለዲጂታል የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ተመራጭ መዳረሻ ማድረግ ከስትራቴጂው ዓላማዎች መካከል መሆኑንም አክለዋል።
ሀገራዊ ዳታዎችንና አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ አዝማሚያዎችን እንዲሁም ሀገራዊ የልማት ፍላጎቶችን መሰረት ያደረጉ መረጃዎችን በማሰባሰብና በመተንተን የዲጂታል ልማቱ ምሰሶዎችንና የትኩረት አቅጣጫዎችን የለየ መሆኑንም ጨምረው አብራርተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026