የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በደቡብ ወሎ ዞን ከ221 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ለማልማት የዘር ሥራ ተጀመረ

Jul 18, 2025

IDOPRESS

ደሴ ፤ ሐምሌ 10/2017(ኢዜአ)፡-በደቡብ ወሎ ዞን በተያዘው የመኸር ወቅት ከ221 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ለማልማት የዘር ሥራ መጀመሩን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በስንዴ ከሚለማው መሬት ከዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል።

በዞኑ ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ፤ በዞኑ ያለው የአየር ንብረትና መልክአምድር ስንዴን በስፋት ለማምረት የተመቸ መሆኑን ለኢዜአ ተናግረዋል።

በዚህም በምርት ዘመኑ እርሻ ማሳውን ደጋግሞ በማረስና የግብዓት አቅርቦት ዝግጅት በማድረግ ከ221 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ለማልማት የዘር ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል።

ከሚለማው መሬትም 145 ሺህ ሄክታር የሚሆነው በኩታ ገጠም ጠቁመው፤ ይህም ግብዓት ለማቅረብ፣ ለድጋፍ፣ በጋራ ለመዝራትና ተባይ ለመከላከል ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።


ከስንዴ ልማቱም ከዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸው፤ አርሶ አደሩ በምግብ ራሱን ከመቻል ባሻገር ለገበያ የሚቀርብ ትርፍ ምርት እንዲያመርት እየተበረታታ መሆኑን አመልክተዋል።

አርሶ አደር አሊ የሱፍ በዞኑ ከለላ ወረዳ የ02 ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ፤ ከአንድ ሄክታር የሚበልጥ መሬታቸውን በኩታ ገጠም ስንዴ ለማልማት የዘር ሥራ መጀመራቸው ገልጸዋል።

ለስንዴ ልማት በቂ ማዳበሪያ ከማግኘታቸው ባለፈ የግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ እያደረጉላቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም የተሻለ በማምረት ከራሳቸው አልፎ ለገበያም ለማቅረብ እየሰራሁ ነው ብለዋል።

በግብርና ባለሙያ ታግዘው የስንዴ ዘር ሥራ መጀመራቸውን የተናገሩት ደግሞ በመቅደላ ወረዳ የ06 ቀበሌ አርሶ አደር አብዱ ኑርዬ ናቸው።

ከግማሽ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ በማልማት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት ጠንክረው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

የኩታገጠም ልማት ግብዓት ቅድሚያ ማግኘታቸው፣ በባለሙያ መደገፋቸውና በጋራ በመዝራት ሰብል መንከባከብ እንዲችሉ ምቹ መደላድል እንደፈጠረላቸው አርሶ አደሮቹ ተናግረዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን በ2017/2018 የመኸር ወቅት በአጠቃላይ 432 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብል በማልማት 15 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026