
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 12/2017 (ኢዜአ):-የስታርት አፕ አዋጅ የዜጎችን የፈጠራ ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር የሚያስችል መሆኑን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተናገሩ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ሀሙስ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የስታርትአፕ አዋጅን ማፅደቁ ይታወቃል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) የአዋጁን መፅደቅ አስመልክተው ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸው ኢትዮጵያ የብዙሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ ግንባታ በመንደፍ እየሰራች መሆኑን አንስተው በዚህም ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።
የፈጠራ ሃሳቦችም እንደ ሌሎች ዘርፎች ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ መሰረት እንዲሆኑ ለማስቻል አዋጅ መዘጋጀቱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
አዋጁ ምቹ የስታርትአፕ ስነ-ምህዳርን በመፍጠር ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታው መሰረት እንዲሆን ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩልም ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ያላቸውን እምቅ አቅም የበለጠ አውጥተው ለሀገር እድገት እንዲያውሉ አስፈላጊ በመሆኑ አዋጁ መዘጋጀቱንም አብራርተዋል።
የጸደቀው አዋጅ የስታርትአፕ ስነ -ምህዳሩን ለማጎልበት የሚያስችል ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።
በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች እድሎችን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
ዜጎች ያላቸው ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት እንዲቀይሩ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ሰለመሆኑን ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የስታርትአፕ ስነ ምህዳር ተወዳዳሪ እንድትሆን የሚያስችል መሆኑን ተናግረው፤ ግዙፍ የሆኑ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችን ለመፍጠር የሚያስችል አዋጅ መሆኑንም ገልጸው፤ ለሀገር የሚያበረክተው አስተዋፅኦም ከፍተኛ በመሆኑ ለውጤታማነቱ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026