የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አዋጁ የዜጎችን የፈጠራ ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር የሚያስችል ነው

Jul 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 12/2017 (ኢዜአ):-የስታርት አፕ አዋጅ የዜጎችን የፈጠራ ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር የሚያስችል መሆኑን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተናገሩ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ሀሙስ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የስታርትአፕ አዋጅን ማፅደቁ ይታወቃል።

የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) የአዋጁን መፅደቅ አስመልክተው ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸው ኢትዮጵያ የብዙሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ ግንባታ በመንደፍ እየሰራች መሆኑን አንስተው በዚህም ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

የፈጠራ ሃሳቦችም እንደ ሌሎች ዘርፎች ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ መሰረት እንዲሆኑ ለማስቻል አዋጅ መዘጋጀቱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

አዋጁ ምቹ የስታርትአፕ ስነ-ምህዳርን በመፍጠር ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታው መሰረት እንዲሆን ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል።

በሌላ በኩልም ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ያላቸውን እምቅ አቅም የበለጠ አውጥተው ለሀገር እድገት እንዲያውሉ አስፈላጊ በመሆኑ አዋጁ መዘጋጀቱንም አብራርተዋል።

የጸደቀው አዋጅ የስታርትአፕ ስነ -ምህዳሩን ለማጎልበት የሚያስችል ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።

በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች እድሎችን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

ዜጎች ያላቸው ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት እንዲቀይሩ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ሰለመሆኑን ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የስታርትአፕ ስነ ምህዳር ተወዳዳሪ እንድትሆን የሚያስችል መሆኑን ተናግረው፤ ግዙፍ የሆኑ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችን ለመፍጠር የሚያስችል አዋጅ መሆኑንም ገልጸው፤ ለሀገር የሚያበረክተው አስተዋፅኦም ከፍተኛ በመሆኑ ለውጤታማነቱ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025