
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 12/2017 (ኢዜአ):-የስታርት አፕ አዋጅ የዜጎችን የፈጠራ ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር የሚያስችል መሆኑን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተናገሩ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ሀሙስ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የስታርትአፕ አዋጅን ማፅደቁ ይታወቃል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) የአዋጁን መፅደቅ አስመልክተው ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸው ኢትዮጵያ የብዙሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ ግንባታ በመንደፍ እየሰራች መሆኑን አንስተው በዚህም ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።
የፈጠራ ሃሳቦችም እንደ ሌሎች ዘርፎች ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ መሰረት እንዲሆኑ ለማስቻል አዋጅ መዘጋጀቱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
አዋጁ ምቹ የስታርትአፕ ስነ-ምህዳርን በመፍጠር ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታው መሰረት እንዲሆን ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩልም ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ያላቸውን እምቅ አቅም የበለጠ አውጥተው ለሀገር እድገት እንዲያውሉ አስፈላጊ በመሆኑ አዋጁ መዘጋጀቱንም አብራርተዋል።
የጸደቀው አዋጅ የስታርትአፕ ስነ -ምህዳሩን ለማጎልበት የሚያስችል ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።
በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች እድሎችን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
ዜጎች ያላቸው ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት እንዲቀይሩ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ሰለመሆኑን ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የስታርትአፕ ስነ ምህዳር ተወዳዳሪ እንድትሆን የሚያስችል መሆኑን ተናግረው፤ ግዙፍ የሆኑ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችን ለመፍጠር የሚያስችል አዋጅ መሆኑንም ገልጸው፤ ለሀገር የሚያበረክተው አስተዋፅኦም ከፍተኛ በመሆኑ ለውጤታማነቱ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025