የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አዋጁ የዜጎችን የፈጠራ ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር የሚያስችል ነው

Jul 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 12/2017 (ኢዜአ):-የስታርት አፕ አዋጅ የዜጎችን የፈጠራ ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየር የሚያስችል መሆኑን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ተናገሩ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ሀሙስ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ የስታርትአፕ አዋጅን ማፅደቁ ይታወቃል።

የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) የአዋጁን መፅደቅ አስመልክተው ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸው ኢትዮጵያ የብዙሃ ዘርፍ የኢኮኖሚ ግንባታ በመንደፍ እየሰራች መሆኑን አንስተው በዚህም ስኬቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

የፈጠራ ሃሳቦችም እንደ ሌሎች ዘርፎች ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ መሰረት እንዲሆኑ ለማስቻል አዋጅ መዘጋጀቱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

አዋጁ ምቹ የስታርትአፕ ስነ-ምህዳርን በመፍጠር ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታው መሰረት እንዲሆን ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል።

በሌላ በኩልም ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ያላቸውን እምቅ አቅም የበለጠ አውጥተው ለሀገር እድገት እንዲያውሉ አስፈላጊ በመሆኑ አዋጁ መዘጋጀቱንም አብራርተዋል።

የጸደቀው አዋጅ የስታርትአፕ ስነ -ምህዳሩን ለማጎልበት የሚያስችል ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።

በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን በመፍታት ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች እድሎችን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

ዜጎች ያላቸው ሃሳብ ወደ ተጨባጭ ውጤት እንዲቀይሩ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ሰለመሆኑን ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የስታርትአፕ ስነ ምህዳር ተወዳዳሪ እንድትሆን የሚያስችል መሆኑን ተናግረው፤ ግዙፍ የሆኑ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችን ለመፍጠር የሚያስችል አዋጅ መሆኑንም ገልጸው፤ ለሀገር የሚያበረክተው አስተዋፅኦም ከፍተኛ በመሆኑ ለውጤታማነቱ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026