የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የ2017 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ የማንሠራራት ዘመን መነሻ የሆኑ ውጤታማ ተግባራት የተከናወኑበት ዓመት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Jul 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017(ኢዜአ)፦ የ2017 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ የማንሠራራት ዘመን መነሻ የሆኑ ውጤታማ ተግባራት የተከናወኑበት ዓመት መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡

በ2018 በጀት ዓመትም በሁሉም ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠልና በጠንካራ መሠረት ላይ የማጽናት ስራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል፡፡

የፌደራል ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ የ2017 በጀት ዓመት በብዙ መልኩ የኢትዮጵያ የብልጽግና ታሪክ እጥፋት የተመዘገበበት ዓመት መሆኑን ገልጸዋል፡፡


በጀት ዓመቱ በሁሉም መስኮች የኢትዮጵያ የማንሠራራት ዘመን መነሻ እንደነበር አንስተው ስኬታማና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የተከናወነበት ዓመት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በውጤቱም በአምራች፣ በግብርና፣ በአገልግሎትና በማዕድን እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ታሪካዊ አፈጻጸሞች መመዝገባቸውን ጠቁመዋል፡፡

በከተሞች እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደርና ሌሎች ልማቶች ውጤት ማምጣት መጀመራቸውን ጠቁመው፤ በትምህርት፣ በጤና፣ በፍትሕና አስተዳደር እንዲሁም በዲፕሎማሲው መስክ አመርቂ ውጤቶች እንደተመዘገቡ አብራርተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በአመቱ ከ150 በላይ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ኮንፍረንሶችን በማስተናገድ ለቱሪዝም የተመቸች መዳረሻ መሆኗን በተግባር ማስመስከሯንም ገልጸዋል፡፡


በአዲሱ በጀት ዓመት ዕቅድ ባለፈው ዓመት በጠንካራ የሪፎርምና የዕቅድ አተገባበር የተገኙትን የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የዋጋ ማረጋጋት፣ የሀገር ውስጥ ገቢ መሰብሰብ እና የወጪ ንግድ ዕድገትን የበለጠ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡

ከማክሮ ኢኮኖሚ እና ከአምራች ዘርፎች አኳያም የተመዘገቡ መልካም ጅምሮችን የማስቀጠልና በጠንካራ መሠረት ላይ የማጽናት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል፡፡


የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ውጤታማ ስራዎችን በማከናወን ላይ ትገኛለች ብለዋል፡፡

በዚህም ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አኳያ ውጤታማ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በአዲሱ በጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

በተያዘው በጀት ዓመት በተለይም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የስራ ዕድል በሰፊው መፍጠር፣ የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ግሽበትን ትርጉም ባለው መልኩ መቀነስ፣ ገቢ የመሰብሰብ፣ ኤክስፖርት የማስፋት ስራዎችን በውጤታማነት በማከናወን ሪፎርሙን በስኬት ለማስቀጠል እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025