
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017(ኢዜአ)፦ የ2017 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ የማንሠራራት ዘመን መነሻ የሆኑ ውጤታማ ተግባራት የተከናወኑበት ዓመት መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡
በ2018 በጀት ዓመትም በሁሉም ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠልና በጠንካራ መሠረት ላይ የማጽናት ስራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል፡፡
የፌደራል ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከፌደራል ተቋማት አመራሮች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፤ የ2017 በጀት ዓመት በብዙ መልኩ የኢትዮጵያ የብልጽግና ታሪክ እጥፋት የተመዘገበበት ዓመት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በጀት ዓመቱ በሁሉም መስኮች የኢትዮጵያ የማንሠራራት ዘመን መነሻ እንደነበር አንስተው ስኬታማና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የተከናወነበት ዓመት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በውጤቱም በአምራች፣ በግብርና፣ በአገልግሎትና በማዕድን እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ታሪካዊ አፈጻጸሞች መመዝገባቸውን ጠቁመዋል፡፡
በከተሞች እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደርና ሌሎች ልማቶች ውጤት ማምጣት መጀመራቸውን ጠቁመው፤ በትምህርት፣ በጤና፣ በፍትሕና አስተዳደር እንዲሁም በዲፕሎማሲው መስክ አመርቂ ውጤቶች እንደተመዘገቡ አብራርተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአመቱ ከ150 በላይ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ኮንፍረንሶችን በማስተናገድ ለቱሪዝም የተመቸች መዳረሻ መሆኗን በተግባር ማስመስከሯንም ገልጸዋል፡፡

በአዲሱ በጀት ዓመት ዕቅድ ባለፈው ዓመት በጠንካራ የሪፎርምና የዕቅድ አተገባበር የተገኙትን የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የዋጋ ማረጋጋት፣ የሀገር ውስጥ ገቢ መሰብሰብ እና የወጪ ንግድ ዕድገትን የበለጠ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡
ከማክሮ ኢኮኖሚ እና ከአምራች ዘርፎች አኳያም የተመዘገቡ መልካም ጅምሮችን የማስቀጠልና በጠንካራ መሠረት ላይ የማጽናት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል፡፡

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ውጤታማ ስራዎችን በማከናወን ላይ ትገኛለች ብለዋል፡፡
በዚህም ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አኳያ ውጤታማ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን ጠቁመው፤ በአዲሱ በጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡
በተያዘው በጀት ዓመት በተለይም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ፣ የስራ ዕድል በሰፊው መፍጠር፣ የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ግሽበትን ትርጉም ባለው መልኩ መቀነስ፣ ገቢ የመሰብሰብ፣ ኤክስፖርት የማስፋት ስራዎችን በውጤታማነት በማከናወን ሪፎርሙን በስኬት ለማስቀጠል እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026