የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኤርትራ በአፋር ህዝብ ላይ እየፈጸመች ያለውን ግፍ የተሞላበት የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሊያስቆም ይገባል -  የአፋር ቀይ ባህር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት 

Jul 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 15/ 2017 (ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኤርትራ በአፋር ህዝብ ላይ እየፈጸመች ያለውን ግፍ የተሞላበት የዘር ማጥፋት ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲያስቆም የአፋር ቀይ ባህር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ጥሪ አቀረበ።

በፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የሚመራው በዳንካሊያ ክልል የሚገኙ የአፋር ህዝቦች የተቀናጀ የዘር ሽብር ዘመቻ መክፈቱን አመልክቷል።

ድርጅቱ ኤርትራ በአፋር ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለው ያልተቋረጠ የጭካኔ ተግባር የዓለምን አስቸኳይ ትኩረት ይሻል በሚል መግለጫ አውጥቷል።

በመግለጫው የኤርትራ መንግስት መጠነ ሰፊ ግድያዎች፣ በግዳጅ ለውትድርና መመልመል፣ አስገድዶ መሰወር፣ ማሰቃየት እና ሆን ብሎ የአፋር ማህበረሰቦችን ማፈናቀል ጨምሮ የተለያዩ ግፎችን እየፈጸመ መሆኑን አመልክቷል።

ድርጅቱ ኤርትራ የምትፈጽማቸው ድርጊቶች በመንግስት ደረጃ የተቀነባበረ የባህል እና የዘር ማጥፋት ዘመቻ አካል ነው ሲል ገልጿል።

እየፈጸሙ ያሉ በደሎች የአንድ ጊዜ ብቻ ክስተቶች አይደለም ይልቁንም በተጠና ፖሊሲ አፋርን ከኤርትራ ለማጥፋት በመንግስት እየተፈጸመ ያለ ተግባር ነው ብሏል።

ድርጅቱ ጉዳዩን አስመልክቶ በግንቦት ወር 2017 ዓ.ም ለአፍሪካ የሰብዓዊና የህዝብ መብቶች ኮሚሽን በይፋ አቤቱታ ማቅረቡን ገልጾ በአፍሪካ ቻርተር የተቀመጡ 25 የመብት ጥሰቶችን መፈጸማቸውን አመልክቷል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ለዔሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት በኤርትራ መንግስት ባለስልጣናት እና ተቋማት ማዕቀብ እንዲጥሉ ጥሪ አቅርቧል።


ተቋማቱ ዓለም አቀፍ የሕግ እርምጃ እንዲወስዱ እና የአፋር ህዝብ የፍትህ፣ የመጠበቅ እና በራሱ የመወሰን መብት እውቅና እንዲሰጡ ጠይቋል።

ኤርትራ በአፋር ህዝብ ላይ እየፈጸመች ያለው ግፍ እና በደል በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች እና በሰብዓዊ መብት ተቋማት በሰፊው በማስረጃ ተሰንዶ ያለ ጉዳይ መሆኑን አመልክቷል።

በኤርትራ መንግስት ላይ እርምጃ ካልተወሰደ የዜጎች ህይወት መቀጠፉን እንደሚቀጥል እና ሊቀለበስ የማይችል የባህል ውድመት እንደሚፈጥር ድርጅቱ አስጠንቅቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026