
ታርጫ፣ ሐምሌ 15/2017 (ኢዜአ) :- የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ለ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል ከ28 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጽድቋል።
የክልሉ ምክር ቤት በታርጫ ከተማ እያካሄደ በሚገኘው 8ኛው መደበኛ ጉባኤ የሁለተኛ ቀን ውሎው በክልሉ ምክር ቤት ለ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል ከ28 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፅድቋል።
በክልሉ ምክር ቤት የፋይናንስና በጀት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ የኋላሸት በላይነህ፤ ቋሚ ኮሚቴው ውይይት ካደረገ በኋላ በጀቱ እንዲፀድቅ መወሰኑን ተናግረዋል።

የተያዘውን በጀት ለታለመለት አላማ ማዋል ላይ ሁሉም መዋቅሮች ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በጀቱ በዋናነት ለድህነት ቅነሳ ስራዎች፣ ለዘላቂ ልማት፣ ለስራ እድል ፈጠራና ለሌሎች አገልግሎቶች እንደሚውልም ተናግረዋል።
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወሰነች ቶማስ በሰጡት ማብራሪያ የበጀቱ ምንጭ የክልሉ የውስጥ ገቢ፣ ከፌደራል መንግስት የሚሰጥ ድጎማ እና ከሌሎች የገቢ ምንጮች እንደሆነም ገልፀዋል።

በጀቱ አምና ከተበጀተው ጋር ሲነፃፀር 45 በመቶ እድገት እንዳለው አንስተው፣ ከአጠቃላይ በጀቱ ውስጥ 18 ቢሊዮን 257 ሚሊዮን 214 ብር በክልሉ የውስጥ ገቢ የሚሸፈን መሆኑን ተናግረዋል።
ሁሉም ዞኖች የገቢ አሰባሰብ አቅማቸውን ማሳደግ፣ በጀቱን በተገቢው ማስተዳደርና ግልፅነት መፍጠር ላይ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩም ኃላፊዋ አሳስበዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026