
ታርጫ፣ ሐምሌ 15/2017 (ኢዜአ) :- የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ለ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል ከ28 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጽድቋል።
የክልሉ ምክር ቤት በታርጫ ከተማ እያካሄደ በሚገኘው 8ኛው መደበኛ ጉባኤ የሁለተኛ ቀን ውሎው በክልሉ ምክር ቤት ለ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል ከ28 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፅድቋል።
በክልሉ ምክር ቤት የፋይናንስና በጀት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ የኋላሸት በላይነህ፤ ቋሚ ኮሚቴው ውይይት ካደረገ በኋላ በጀቱ እንዲፀድቅ መወሰኑን ተናግረዋል።

የተያዘውን በጀት ለታለመለት አላማ ማዋል ላይ ሁሉም መዋቅሮች ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በጀቱ በዋናነት ለድህነት ቅነሳ ስራዎች፣ ለዘላቂ ልማት፣ ለስራ እድል ፈጠራና ለሌሎች አገልግሎቶች እንደሚውልም ተናግረዋል።
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ወሰነች ቶማስ በሰጡት ማብራሪያ የበጀቱ ምንጭ የክልሉ የውስጥ ገቢ፣ ከፌደራል መንግስት የሚሰጥ ድጎማ እና ከሌሎች የገቢ ምንጮች እንደሆነም ገልፀዋል።

በጀቱ አምና ከተበጀተው ጋር ሲነፃፀር 45 በመቶ እድገት እንዳለው አንስተው፣ ከአጠቃላይ በጀቱ ውስጥ 18 ቢሊዮን 257 ሚሊዮን 214 ብር በክልሉ የውስጥ ገቢ የሚሸፈን መሆኑን ተናግረዋል።
ሁሉም ዞኖች የገቢ አሰባሰብ አቅማቸውን ማሳደግ፣ በጀቱን በተገቢው ማስተዳደርና ግልፅነት መፍጠር ላይ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩም ኃላፊዋ አሳስበዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026