የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የውጭ ምንዛሬ አቅምን ለማሳደግ በተከናወነ ሥራ ውጤት ተመዝግቧል

Jul 23, 2025

IDOPRESS

አርባምንጭ ፤ ሐምሌ 15/ 2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የተኪ ምርቶችን ሚና በማጉላት የውጭ ምንዛሬ አቅምን ለማሳደግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።

ኮርፖሬሽኑ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ለማሳካት ከ40 በላይ አምራች ኢንተርፕራይዞች እና አልሚ ባለሀብቶች የሚሳተፉበት ዐውደ ርዕይና ባዛር በአርባ ምንጭ ከተማ ማዘጋጀቱም ተመላክቷል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ተቋሙ በተሰጠው ተልዕኮ መሠረት በተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ እና በአምራች ኢንተርፕራይዞች ክላስተር ልማት ውጤታማ ስራ እያከናወነ ይገኛል።

ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የተኪ ምርቶችን ሚና በማጉላት የውጭ ምንዛሬ አቅምን ለማሳደግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በአምራች ኢንተርፕራይዞችና አልሚ ባለሀብቶች የጨርቃ ጨርቅ፣ የዘይትና የሞሪንጋ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ማግኘት ተችሏል ብለዋል።

በአንጻሩም በተኪ ምርት 30 ሚሊዮን ብር የሚሆን የውጭ ምንዛሬን ማዳን መቻሉን ዋና ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።

በክልሉ ዲላ እና ይርጋጨፈ ሁለት የመካከለኛ ግብርና ኢንዱስትሪ ፓርኮች መኖራቸውን ጠቅሰው የዲላ ግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ በበጀት ዓመቱ 50 ሺህ ሊትር ድፍድፍ የአቮካዶ ዘይት አምርቶ ወደ ውጭ መላኩን ተናግረዋል።

በቡና፣ በወተትና በሌሎች ምርቶች ማቀነባበር ስራ ላይ የሚሰማራው የይርጋጨፌ ግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ በ2018 ዓ/ም በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል በክልሉ በ9 ከተሞች በሚገኙ 17 ክላስተር ማዕከላት 150 ሼዶች መኖራቸውን ጠቅሰው ከነዚህም ውስጥ 126ቱ አምራች ኢንተርፕራይዞች በተለያዩ የሥራ መስኮች ላይ መሰማራታቸውን አስረድተዋል።

ኢንተርፕራይዞቹ በእንጨትና ብረታ ብረት፣ በአግሮ ፕሮሴሲንግ፣ በኬሚካል ውጤቶች፣ በሽመና፣ በቆዳና ሌጦ እንዲሁም በጨርቃ ጨርቅና ሌሎች ስራዎች ላይ በመሰማራት ውጤታማ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል።

ኮርፖሬሽኑ ከ40 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች እና አልሚ ባለሀብቶች የሚሳተፉበት ክልል አቀፍ ባዛርና ዐውደ ርዕይን የፊታችን ሐምሌ 17 እና 18 ቀን 2017 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ከተማ ለማካሄድ ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።

ይህም ኢንተርፕራይዞች እና አልሚ ባለሀብቶች ምርቶቻቸውን በማስተዋወቅ የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ ታስቦ መዘጋጀቱንም አመልክተዋል።

በመርሃ-ግብሩ ላይም በ39 ሚሊዮን ብር የተገነባው የአርባምንጭ ከተማ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ሼድ ምረቃ የሚካሄድ ሲሆን የአረንጓዴ አሻራ ልማት እና የኢንዱስትሪ ልማት የምክክር መድረክ አጀንዳዎች እንደሚኖሩም ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025